Sunday, August 26, 2012

ከሞቱ ዜና ጋር በተያያ

ማሕሌት ፋንታሁን

የዚህ ጽሑፍ ዋና ቅጂ በኢትዮጵያ እንዳይነበብ በታገደው የዞን ዘጠኝ ጦማር ላይ ይገኛል፡፡
የመለስን ሞት ተከትሎ ብዙ እየተባሉ ያሉ ነገሮች አሉ፡፡ ሬድዮና ቴሌቭዥኑ ሙሉ ሰዓቱን ጠ/ሩ በህይወት ዘመናቸው ያከናወኗቸውን ተግባራት እና ያደረጉትን ንግግር  ሃዘን ውስጥ የመክተት ብቃት ካላቸው ክላሲካል ሙዚቃ እና ዋሽንት ጋር በማቀነባበር በማሰማት ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የጠ/ሩን ሞት በተመለከተ በተለያዩ በአገራችን ክልሎች የሚገኙ ነዋሪዎችና ታዋቂ ሰዎች የተሰማቸውን  መሪር ሃዘን እና በምን አይነት ሁኔታ እያዘኑ እንዳሉ እየተከታተሉ ዘገባዎችን ያቀርባሉ፡፡ ይህ ሁኔታ ስርአተ ቀብሩ እስኪፈፀም ድረስ እንደሚቆይ ቢነገርም ከዛ በኋላም ምናልባት እንዳሁኑ ሙሉ የፕሮግራማቸውን ሰዓት ባይሆንም እስከተወሰነ ጊዜ በተመሳሳይ ሁኔታ ሊቀጥል እንደሚችል ጥርጣሬ አለኝ፡፡ ጋዜጣና መፅሄቶችም ስለመለስ በሚያወሩ ፅሁፎች እንዲሁም ከተለያዩ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የተላኩ የሃዘን መግለጫዎችን ከታዋቂ ሰዎች የተሰጠ አስተያየት ጋር ይዘው ወጥተዋል፡፡

ፌስቡክ መንደር ደግሞ ጠ/ሩ የመሞታቸው ዜና በአገር ውስጥ ሚዲያ እስከተነገረበት ሰዓት ድረስ አትሌቶቻችን በለንደን ኦሎምፒክ በተሳተፉበት ወቅት ስለተገኙት ውጤቶች ከተወራባቸው ውስን ቀናት ውጪ ለተከታታይ ስልሳ ቀናት ወሬው ሁሉ በአብዛኛው የመለስ የጤና ሁኔታ ነበር ብል ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ የተለያዩ ምንጮችን በመጥቀስ መሞቱን ሲዘግቡ የነበሩ ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉ ኢትዮጵያዊ ሚዲያዎች ነበሩ፡፡በጠና መታመሙን እና ከዚህ በኋላ ብዙ ጊዜ እንደማይቆይ የሚያትቱ ወሬዎችን ያስነበቡን የውጪ ደህረ ገፆችም የነበሩ ሲሆን በአንፃሩ ደግሞ በአገር ውስጥ የሚገኙ ጋዜጦች በጣም እስክንገረም ድረስ እርስ በርሱ የሚጣረስ መረጃ ሲያቀርቡ ነበር፡፡ ከኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስቴር የሚሰጡ መግለጫዎችም እንዲሁ ግልፅነት የጎደላቸው እና ሙሉ ምላሽ የሚሰጡን አይነት አልነበሩም፡፡ በስተመጨረሻም አቶ በረከት የመለስ ጤንነት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ እና ለአዲስ አመት መጥተው እንኳን አደረሳችሁ እንደሚሉን ነግረውን ነበር የቆምነው፡፡

ሞቱ በአገራችን ሚዲያ እስከተነገረበትም እለት ድረስ በፌስቡክ እና በተለያዩ የሶሻል ሚዲያዎች ያሉ ተሳታፊዎች ‹አልሞተም›፣ ‹ሞቷል› እና ‹በጠና ታሟል› ብለው ማሳመኛ የሚሉትን ሃሳቦች እያነሱ በንቃት ሲወያዩ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ከዚህም አልፈው ድህረ መለስ ትንታኔ ሲሰጡ እና የተለያዩ ግምቶቻቸውን ሲያካፍሉም ነበር፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የመለስ ሞት በአገራችን ሚዲያ አብዛኛው ሰው ባልጠበቀበት ሰዓት ሲገለፅ ውይይቱ በመለስ ሞት ማዘንን እና አለማዘንን በመግለፅ ተቀየረ፡፡ ያዘኑት ያላዘኑትን ባለማዘናቸው፤ ያላዘኑቱ ደግሞ ያዘኑትን በማዘናቸው መውቀስና መተቸት ተጀመረ፡፡እስካሁንም ድረስ ይህ መወቃቀስ አላቆመም፡፡ በበኩሌ ‹ማዘን› ወይም ‹አለማዘን› ከውስጥ የሚመነጭ ስሜት እስከሆነ ድረስ ባለመስማማት መለያየት ሲቻል ‹ማዘን ነበረብህ› ወይም ‹ማዘን አልነበረብህም› ብሎ መፍረድ እና ያልተገቡ ቃላትን መወራወር ትክክል አይመስለኝም፡፡ ደግሞም ማዘንም ያለማዘንም የግለሰብ መብት እና ምርጫ ናቸው እንጂ ግዴታ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ በፌስቡክ በምናያቸው ውይይቶች ላይ የሚስተዋሉት ወቀሳዎችና ትችቶች ግፋ ቢል ስድብ ቢታከልባቸው ነው፡፡ በርግጥ እኛ ሳናቅ በስውር የተፈፀሙ ወይም የሚፈፀሙ ከስድብ የዘለሉ ነገሮች ተከስተውም ሊሆን ይችላል፡፡ በማረሚያ ቤቶችና በአንዳንድ ቦታዎች ግን ነገሩ አለአግባብ ተካብዶና ትኩረት ተሰጥቶት እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውን የሚያመላክቱ ነገሮች እየሰማን ነው፡፡


ሰሞኑን ርዕዮትን ለመጠየቅ ማረሚያ ቤት በሄድኩበት ሰዓት የሰማሁት ነገር የሚያስደነግጥ ነው፡፡ የመለስ ሞት ከተነገረ በኋላ ያልተለመዱ ማስፈራሪያዎችና ዛቻዎች እየሰማች እንደሆነ በማዘን ነግራኛለች፡፡ ሌሎቹ እስረኞች ‹እነዚህን ልጆች ከመግደላችን በፊት ውሰዱልን› ብለውናል ተብለው እሷና እማዋይሽ የተባለች ሌላ ፍርደኛ ከነበሩበት ክፍል እንዲወጡ ተደርገው ሁለቱም ወደተለያየ ክፍል እንደተላኩና ከማያቋቸው በቀጠሮ ላይ ያሉ እስረኞች ከሚገኙበት ክፍል እንዲዛወሩም ተደርገዋል፡፡ ከተነገራቸው ማስፈራሪያ እና ወደ አዲሱ ክፍል ተለያይተው በመወሰዳቸው ምክንያት እንቅስቃሴያቸው ሁሉ በከፍተኛ ስጋት የተሞላ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ለወትሮው ፈገግታ በተሞላበት ፊት እና ብሩህ ተስፋዋን በሚያመላክት የራስ መተማመን መንፈስ ጠያቂዎቿን የማዋራት እና የማጫወት ልምድ የነበራት ርዕዮት ሰሞኑን ከደረሰባት ዛቻ እና ማስፈራሪያ በመነሳት ያደረባትን ስጋት ስትናገር እንባዋን መቆጣጠር አልተቻላትም፡፡ ከመለስ ሞት ዜና መነገር ጋር በተያያዘ ሆነም ሌላ ያፈፀመችው ጥፋት እንደሌለና ምናልባትም ግን የመለስ ፎቶ ያለበትን ካኔቴራ በ120 ብር ግዙ ሲባል መግዛት እንደማትፈልግ መናገሯ እንዲሁም ይህን መንግስት በመተቸት የምትታወቅ በመሆኗ ምክንያት   ይህ ሁኔታ እንደተከሰተባት የምትጠረጥር ሲሆን ‹‹ይህን የምነግራችሁ የሞትና የሽረት ጉዳይ ስለሆነ እንድታውቁት ነው እንጂ ከዚህ በፊትም ምንም አልነበረም ማለት አይደለም›› ብላለች፡፡ 

በተያያዘ ዜናም ባለፈው አርብ ፍኖተ ጋዜጣ በልዩ እትሙ በቅሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ‹መለስ ሞተ ተብሎ ሲነገር ሌሎቹ ሲያለቅሱ አንተ ስቀሃል› ተብሎ በእሰረኞች ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰበት እና ባለቤቱ ከፖሊሶች ‹ካልመከርሽው እስረኞች ሊገሉት ይችላሉ› የሚል ማስጠንቀቂያ እንደደረሳቸው  እንዲሁም ከጠ/ሚር መለስ ሞት ጋር በተያያዘ የአንድነት አባላት እየታሰሩ መሆኑን አስነብቦናል፡፡ ወዴት እየተኬደ ነው ትላላችሁ? እነዚህ ሰዎች መለስ ይማረን ሊያስብሉን ይሆን ይሆን?
በ<a href="http://www.facebook.com/mahifantish.wube">ማሕሌት ፋንታሁን</a>

የዚህ ጽሑፍ ዋና ቅጂ በኢትዮጵያ እንዳይነበብ በታገደው የዞን ዘጠኝ ጦማር ላይ ይገኛል፡፡

<photo id="1" />የመለስን ሞት ተከትሎ ብዙ እየተባሉ ያሉ ነገሮች አሉ፡፡ ሬድዮና ቴሌቭዥኑ ሙሉ ሰዓቱን ጠ/ሩ በህይወት ዘመናቸው ያከናወኗቸውን ተግባራት እና ያደረጉትን ንግግር  ሃዘን ውስጥ የመክተት ብቃት ካላቸው ክላሲካል ሙዚቃ እና ዋሽንት ጋር በማቀነባበር በማሰማት ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የጠ/ሩን ሞት በተመለከተ በተለያዩ በአገራችን ክልሎች የሚገኙ ነዋሪዎችና ታዋቂ ሰዎች የተሰማቸውን  መሪር ሃዘን እና በምን አይነት ሁኔታ እያዘኑ እንዳሉ እየተከታተሉ ዘገባዎችን ያቀርባሉ፡፡ ይህ ሁኔታ ስርአተ ቀብሩ እስኪፈፀም ድረስ እንደሚቆይ ቢነገርም ከዛ በኋላም ምናልባት እንዳሁኑ ሙሉ የፕሮግራማቸውን ሰዓት ባይሆንም እስከተወሰነ ጊዜ በተመሳሳይ ሁኔታ ሊቀጥል እንደሚችል ጥርጣሬ አለኝ፡፡ ጋዜጣና መፅሄቶችም ስለመለስ በሚያወሩ ፅሁፎች እንዲሁም ከተለያዩ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የተላኩ የሃዘን መግለጫዎችን ከታዋቂ ሰዎች የተሰጠ አስተያየት ጋር ይዘው ወጥተዋል፡፡

ፌስቡክ መንደር ደግሞ ጠ/ሩ የመሞታቸው ዜና በአገር ውስጥ ሚዲያ እስከተነገረበት ሰዓት ድረስ አትሌቶቻችን በለንደን ኦሎምፒክ በተሳተፉበት ወቅት ስለተገኙት ውጤቶች ከተወራባቸው ውስን ቀናት ውጪ ለተከታታይ ስልሳ ቀናት ወሬው ሁሉ በአብዛኛው የመለስ የጤና ሁኔታ ነበር ብል ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ የተለያዩ ምንጮችን በመጥቀስ መሞቱን ሲዘግቡ የነበሩ ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉ ኢትዮጵያዊ ሚዲያዎች ነበሩ፡፡በጠና መታመሙን እና ከዚህ በኋላ ብዙ ጊዜ እንደማይቆይ የሚያትቱ ወሬዎችን ያስነበቡን የውጪ ደህረ ገፆችም የነበሩ ሲሆን በአንፃሩ ደግሞ በአገር ውስጥ የሚገኙ ጋዜጦች በጣም እስክንገረም ድረስ እርስ በርሱ የሚጣረስ መረጃ ሲያቀርቡ ነበር፡፡ ከኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስቴር የሚሰጡ መግለጫዎችም እንዲሁ ግልፅነት የጎደላቸው እና ሙሉ ምላሽ የሚሰጡን አይነት አልነበሩም፡፡ በስተመጨረሻም አቶ በረከት የመለስ ጤንነት በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ እና ለአዲስ አመት መጥተው እንኳን አደረሳችሁ እንደሚሉን ነግረውን ነበር የቆምነው፡፡

ሞቱ በአገራችን ሚዲያ እስከተነገረበትም እለት ድረስ በፌስቡክ እና በተለያዩ የሶሻል ሚዲያዎች ያሉ ተሳታፊዎች ‹አልሞተም›፣ ‹ሞቷል› እና ‹በጠና ታሟል› ብለው ማሳመኛ የሚሉትን ሃሳቦች እያነሱ በንቃት ሲወያዩ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ከዚህም አልፈው ድህረ መለስ ትንታኔ ሲሰጡ እና የተለያዩ ግምቶቻቸውን ሲያካፍሉም ነበር፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የመለስ ሞት በአገራችን ሚዲያ አብዛኛው ሰው ባልጠበቀበት ሰዓት ሲገለፅ ውይይቱ በመለስ ሞት ማዘንን እና አለማዘንን በመግለፅ ተቀየረ፡፡ ያዘኑት ያላዘኑትን ባለማዘናቸው፤ ያላዘኑቱ ደግሞ ያዘኑትን በማዘናቸው መውቀስና መተቸት ተጀመረ፡፡እስካሁንም ድረስ ይህ መወቃቀስ አላቆመም፡፡ በበኩሌ ‹ማዘን› ወይም ‹አለማዘን› ከውስጥ የሚመነጭ ስሜት እስከሆነ ድረስ ባለመስማማት መለያየት ሲቻል ‹ማዘን ነበረብህ› ወይም ‹ማዘን አልነበረብህም› ብሎ መፍረድ እና ያልተገቡ ቃላትን መወራወር ትክክል አይመስለኝም፡፡ ደግሞም ማዘንም ያለማዘንም የግለሰብ መብት እና ምርጫ ናቸው እንጂ ግዴታ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ በፌስቡክ በምናያቸው ውይይቶች ላይ የሚስተዋሉት ወቀሳዎችና ትችቶች ግፋ ቢል ስድብ ቢታከልባቸው ነው፡፡ በርግጥ እኛ ሳናቅ በስውር የተፈፀሙ ወይም የሚፈፀሙ ከስድብ የዘለሉ ነገሮች ተከስተውም ሊሆን ይችላል፡፡ በማረሚያ ቤቶችና በአንዳንድ ቦታዎች ግን ነገሩ አለአግባብ ተካብዶና ትኩረት ተሰጥቶት እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውን የሚያመላክቱ ነገሮች እየሰማን ነው፡፡

ሰሞኑን ርዕዮትን ለመጠየቅ ማረሚያ ቤት በሄድኩበት ሰዓት የሰማሁት ነገር የሚያስደነግጥ ነው፡፡ የመለስ ሞት ከተነገረ በኋላ ያልተለመዱ ማስፈራሪያዎችና ዛቻዎች እየሰማች እንደሆነ በማዘን ነግራኛለች፡፡ ሌሎቹ እስረኞች ‹እነዚህን ልጆች ከመግደላችን በፊት ውሰዱልን› ብለውናል ተብለው እሷና እማዋይሽ የተባለች ሌላ ፍርደኛ ከነበሩበት ክፍል እንዲወጡ ተደርገው ሁለቱም ወደተለያየ ክፍል እንደተላኩና ከማያቋቸው በቀጠሮ ላይ ያሉ እስረኞች ከሚገኙበት ክፍል እንዲዛወሩም ተደርገዋል፡፡ ከተነገራቸው ማስፈራሪያ እና ወደ አዲሱ ክፍል ተለያይተው በመወሰዳቸው ምክንያት እንቅስቃሴያቸው ሁሉ በከፍተኛ ስጋት የተሞላ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ለወትሮው ፈገግታ በተሞላበት ፊት እና ብሩህ ተስፋዋን በሚያመላክት የራስ መተማመን መንፈስ ጠያቂዎቿን የማዋራት እና የማጫወት ልምድ የነበራት ርዕዮት ሰሞኑን ከደረሰባት ዛቻ እና ማስፈራሪያ በመነሳት ያደረባትን ስጋት ስትናገር እንባዋን መቆጣጠር አልተቻላትም፡፡ ከመለስ ሞት ዜና መነገር ጋር በተያያዘ ሆነም ሌላ ያፈፀመችው ጥፋት እንደሌለና ምናልባትም ግን የመለስ ፎቶ ያለበትን ካኔቴራ በ120 ብር ግዙ ሲባል መግዛት እንደማትፈልግ መናገሯ እንዲሁም ይህን መንግስት በመተቸት የምትታወቅ በመሆኗ ምክንያት   ይህ ሁኔታ እንደተከሰተባት የምትጠረጥር ሲሆን ‹‹ይህን የምነግራችሁ የሞትና የሽረት ጉዳይ ስለሆነ እንድታውቁት ነው እንጂ ከዚህ በፊትም ምንም አልነበረም ማለት አይደለም›› ብላለች፡፡ 

በተያያዘ ዜናም ባለፈው አርብ ፍኖተ ጋዜጣ በልዩ እትሙ በቅሊንጦ ማረሚያ ቤት የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ‹መለስ ሞተ ተብሎ ሲነገር ሌሎቹ ሲያለቅሱ አንተ ስቀሃል› ተብሎ በእሰረኞች ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰበት እና ባለቤቱ ከፖሊሶች ‹ካልመከርሽው እስረኞች ሊገሉት ይችላሉ› የሚል ማስጠንቀቂያ እንደደረሳቸው  እንዲሁም ከጠ/ሚር መለስ ሞት ጋር በተያያዘ የአንድነት አባላት እየታሰሩ መሆኑን አስነብቦናል፡፡ ወዴት እየተኬደ ነው ትላላችሁ? እነዚህ ሰዎች መለስ ይማረን ሊያስብሉን ይሆን ይሆን?

No comments:

Post a Comment