Monday, December 28, 2015

አዲስ አባባ ስለምን ታወዛግባለች

 ዘላለም ክብረት

ሕሩይ ሚናስ አስደናቂ ሰው ነው፡፡ የገበሬ ልጅ፣ በአስራዎቹ መጨረሻ አዲስ አበባ የገባ፡፡ ከዛም የአብነት ተማሪ ሆነና ቅዳሴና ቅኔ ሞካከረ፡፡ እሱ አልሆን ሲለው ጎዳና ወጥቶ ጎዳና አዳሪ ሆነ፡፡ ቀጠለና የለማኝ መሪ (sighted guide) ሆነ፡፡ እሱም ሲያልፍ ‹ለምን አልማርም?› ብሎ ትምህርት ተማረና ዩንቨርሲቲ በገባ በዓመቱ ‹ማርክሲስት› ሆነ፡፡ ትምህርቱንም ለአቢዮቱ ሲባል ተወውና መፅሃፍ ነጋዴ ሆነ፡፡ ማርክሲስት ነጋዴ! ‹ከወገብ በላይ ታቦት፣ ከወገብ በታች ጣኦት› እንዲሉ የትናንት ቀዳሹ ሕሩይ ዛሬ ማርክስዚምን ወደደ፡፡ የሕሩይ ማርክሲዝም ከትናንት ማንነቱ እጅግ በተለየ መንገድ ወሰደው፣ የመፅሃፍ አርታኢነት፡፡ መፅሃፍ ሲያነብ፣ ሲተረጉም፣ ሲፅፍና የአርትኦ ስራ ሲሰራ ውሎ ጫት ይቅማል፤ በዛ ላይ አረቄም ይሞካክራል፡፡ በመጨረሻ አበደ፡፡ ከዛ በኋላ ያለው የሕይወቱ ምዕራፍ ብዙ ያሳዝናል፡፡

በኋላ ከአዕምሮ ሕመሙ ሲያገግም ግን የሚገርም ነገር አደረገ፡፡ ‹እብድ› እያለ ሲያደርጋቸው ነበሩትንና የሚያስታውሳቸውን ነገሮች ሁሉ በተርታ ፅፎ ‹እብዱ› በሚል ርዕስ መፅሃፍ አሳተመ፡፡ ይህ መፅሃፉ ለሕሩይ ከብዙ ስራዎቹ አንዱ ነው፡፡ ስለ አዲስ አበባ ለመፃፍ ከሕሩይ የተሻለ ምሳሌ ማግኝት ይከብዳል፡፡ እሱም ‹ወይ ዐዲስ ዓበባ› በሚል ርዕስ (እውነትን መሰረት ያደረገ) መፅሃፍ ፅፎ አዲስ አበባ ከሩቅ ሲያይዋት ምን እንደምትመስል ይተርካል፡፡ በሕሩይ የገጠር ሕይወት አይን አዲስ አበባ ገነት ነበረች፡፡ ሕሩይ እንዲያውም በመደነቅ ‹‹ለካ የዐዲስ ዓበባን ሰው ፎቶ እያነሱ ነው ወደ ገጠር ‹ምስለ መላዕክትና ሰማዕት› እያሉ የሚልኩልን›› በማለት እሱ ከሚያውቀው ገጠርና ሕዝቡ አንፃር አዲስ አበባ ገነት፣ ነዋሪዎቿም መልዓክት እንደሆኑ ይገልፃል፡፡ ገነት ሆና ከሩቅ የታየችው አዲስ አበባ ሲገባባት ጎዳና ላይ አስተኝታዋላች፣ ‹አቢዮተኛ› አድርጋዋለች፣  አሳብዳ አስለፍልፋዋለች … በስተርጅናውም ‹ከጋራ ኮንዶሚኒየም ቤቶቿ› በአንዱ ይኖር ዘንድ ፈቅዳለታለች፡፡ ሕሩይ አዲስ አባባን ከሩቅ አይቶ ጎምጅቶባታል፡፡ አዲስ አበባን ጉያዋ ስር ሆኖም ተሰቃይቶባታል፡፡ ዛሬ ደግሞ አዲስ አበባ ሕሩይን እንከባከብኻለሁ እያለችው ነው፡፡  ሕሩይ ሚናስ - ራሱን ‹አውግቸው ተረፈ› ብሎ የሰየመ ሰው፡፡

ይህ የሕሩይ ብቻ ታሪክ አይደለም፡፡ የብዙ ኢትዮጵያዊያንም እንጂ፡፡ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ አዲስ አበባን ከከተማም በላይ የስልጣኔ ምልክት አድርጎ ነው የሚቆጥራት፡፡ እንዲያውም ሌሎች ከተሞች የሚለሙት ከአዲስ አበባ የሚመጡ ነዋሪዎች እንዲዝናኑባቸው ሁሉ እስኪመስል ድረስ የሌሎች ከተሞችን ዕድገት ሁሉ ወሳኟ አዲስ አበባ እየሆነች ነው፡፡ ከአዲስ አበባ ውጭ ባሉ አካባቢዎች ‹የአዲስ አበባ እንግዶች መጥተዋል› ከተባለ ነገሩ ትልቅ ነው፡፡ አንዳንዴማ ‹እሷ እኮ አዲስ አበባ ቤት አላት› ሲባል ሁሉ ነው ሃብት የሚቆጠረው፡፡ 

አዲስ አበባ አንድ ከተማ ብቻ ነች ማለት ከባድ ነው፡፡ ከሀገሪቱ አጠቃላይ ሕዝብ 3.6 በመቶው ብቻ ቢሆንም አዲስ አበባ የሚኖረው ቀሪው የሀገሪቱ ሕዝብ ያለ አዲስ አበባ ምንድን ነው? እስኪባል ድረስ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ለተባለው ዓለም የስበት ማዕከል (center of gravity) ናት፡፡ 

Monday, December 21, 2015

Government must stop the killings


The Ethiopian Government is using firearms to crowds of protesters to brutally suppress the large-scale Oromo students who are protesting government’s plan of expanding the capital city, Addis Ababa into Oromia Regional State. Over the last four weeks of sustained protests at least 70 people were killed, hundreds injured and several citizens are arrested. Instead of stepping back and examining the students protest in the context of constitutional framework, the Ethiopian government officials embarked on a propaganda campaign of demonizing the protesters. Particularly, we are disturbed to hear high ranking government officials such as the Prime Minister speak in an intimidating undertone using phrases such as ‘we punish protestors mercilessly’.

Over the last four weeks we believe the government has violated the following articles of the constitution:

1. Article 15 Right to Life  

“Every person has the right to life. No person may be deprived of his life except as a punishment for a serious criminal offence determined by law”. Reports have indicated that at least 70 citizens have been killed by live ammunitions fired by red beret wearing security forces. Countless others are beaten, arrested and are made to live in fear.

2. Article 24 Right to Honor and Reputation
 
“Everyone has the right to respect for his human dignity, reputation and honor.” In a government presser broadcasted on the state owned television the protestors have been called ‘demons’. They are   labeled criminals without any sort of due process of law.

3.       Article 30 Right of Assembly, Demonstration and Petition

“Everyone has the right to assemble and to demonstrate together with others peaceably and unarmed, and to petition.” From reports we have learned that the protests are largely peaceful. From the media reports and the images of the protests being circulating on social media we can witness that citizens are using their constitutional rights of nonviolent tactics such as  silence, turning their back, displaying symbols, putting their crossed hands in the air, marching and parading, but government is using its strong  security forces to disband them.

In this age of information and communication technology attempting to conceal government’s misconducts or refusing to recognize citizens’ constitutional right shall only bring embarrassment to the government that claims it has been elected democratically just six months ago. We believe absolute shutdown of the public space will only lead to further grievances and aggravate the situation. Hence we ask the government to:

 -Stop arresting and killing of innocent civilians

-Instead of shutting the public space the government must allow citizens to exercise their constitutional rights and express their thoughts and opinions about the Master Plan

-End impunity and bring those who have violated the constitutional rights of citizens to justice.

Zone9 has been always advocating for peaceful and non-violent ways of criticizing the government and demanding rights. This peaceful way of advocating for change is the one that we are living for, speak for, arrested for and exiled for too.  We are in solidarity with peaceful protesters and all nonviolent actors who works to bring perpetrators to justice and demands their rights.   


Respect the constitution. 

ሕገ መንግስታዊነት እንዲሰፍን የሚፈሰው ተጨማሪ ደም ይገደብ!

የአዲስ አበባ ከተማና የኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላንን ተቃውመው ሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎች በኦሮሚያ ክልል በርካታ ወረዳዎችና ከተሞች  እያቀረቡት ያለው ሠላማዊ ጥያቄ በሰከነ መንገድ መልስ ለመስጠት ከመሞከር ይልቅ ተመጣጣኝ ያልሆነ ሀይል በመጠቀም ጥያቄውን ለማፈን እየተሞከረ ነው፡፡ በዚህ ሂደትም ብዙዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፣ ለቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ እስካሁን ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ዜጎችም ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ሰሞኑን ከሚወጡት መግለጫዎችና የመንግስት ባለስልጣናት ቃለመጠይቆች እንደተረዳነው  ጥያቄዎቻቸውን በሃይል ለመመከት ከመዛትና ዜጎችን ከሰው በታች አውርዶ ቁጣን በሚጋብዝ መልኩ ከመጥራት በዘለለ ሀላፊነት እንደሚሰማው አካል ለችግሩ መፍትሔ  ለመፈለግ ዝግጁነት እንደሌለ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሁሌም እንዲከበር የምንጠይቀውን የሀገሪቱ ሕጎች ሁሉ የበላይ የሆነውን ሕገ-መንግስት የሚጻረር ነው፡፡
በዚህ ሂደት በጥቂቱ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የሕገ-መንግስቱ አንቀጾች ተጥሰዋል
1.    የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 15 የሕይወት መብት
‹‹ማንኛውም ሰው በሕይወት የመኖር መብት አለው፡፡ ማንኛውም ሰው በሕግ በተደነገገ ከባድ የወንጀል ቅጣት ካልሆነ በስተቀር ሕይወቱን አያጣም፡፡›› ቢልም ከሰላማዊ ሰልፉ ጋር በተያያዘ ከ8 ዓመት ልጅ አንስቶ እስከ የ80 ዓመት አዛውንት ድረስ ሕይወት እየተቀጠፈ ነው፤ እስከዛሬ የሞቱት ሰዎች ቁጥር በሶስተኛ ወገን ማረጋገጥ ባይቻልም ጉዳዬን  በቅርበት የሚከታሉ ሰዎች እንደዘግቡት ወደ መቶ እየተጠጋ ይገኛል፡፡
2.   የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 15 የአካል ደኅንነት መብት
‹‹ማንኛውም ሰው በአካሉ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ የመጠበቅ መብት አለው፡፡ ›› አሁንም ከሰላማዊ ሰልፉ ጋር በተያያዘ በጥይት የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች ቁጥራቸው በርካታ ነው፡፡ ድብደባ እና አላግባብ አንግልት የደረሰባቸውንም ቤት ይቁጠራቸው፡፡
3.   አንቀጽ 24.1 የክብርና የመልካም ስም መብት
‹‹ማንኛውም ሰው ሰብዓዊ ክብሩና መልካም ስሙ የመከበር መብት አለው፡፡ ›› እየሆነ ያለው ዜጎችን አጋንንት እያሉ መጥራት፣ ጥፋተኛ ተብለው በሕግ ያልተፈረደባቸውን አሸባሪ እያሉ ክብራቸውን በሚዲያ መግፈፍ ነው፡፡
4.   አንቀጽ 30.1 የመሰብሰብ፤ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት
‹‹ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና፣ አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ ከቤት ውጭ የሚደረጉ ስብሰባዎችና ሰላማዊ ሰልፎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች በሕዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እንዳይፈጥሩ ለማድረግ ወይም በመካሔድ ላይ ያለ ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ሰላምን፣ ዴሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱ ለማስጠበቅ አግባብ ያላቸው ሥርዓቶች ሊደነገጉ ይችላሉ፡፡ ››  ቢልም መንግስት ይህን የህገ መንግሰቱን አንቀጽ በመጣስ ብዙ ሰብዓዊ ጉዳቶችን አድርሷል፡፡

ዜጎች ለመረጃ ቅርብ በሆኑበት በዚህ ጊዜ መንግስት እያደረጋቸው ያሉትን ተግባራት መካድ፣ እንዲሁም እንደሌሉ አደርጎ ለማስተባበል መሞከር ብዙ ኃላፊነት የሚጠበቅበት መንግስት የሚያሰገምትና ትዝብት ላይ የሚጥል ነው፡፡ ይህ የመንግስት ግዴለሽነት ብዙኃን ዜጎችን እየገፋ ከመስመር እያስወጣ ነው፡፡ ሰላማዊውን የሕዝብ እንቅስቃሴ ወደ አመጽ እና ወደአልተፈለገ ዕልቂት ከመግፋት ይልቅ የተቀናጀ የጋር ማስተር ፕላኑን  መሰረዝ፣ በዚህ ሒደት ጥፋት የፈጸሙ በየደረጃው የሚገኙ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትን ለፍርድ ማቅረብ፣ የግል ተበዳዮችን  መካስና ሌሎች አስፈላጊ የመፍትሔ እርምጃዎችን ሁሉ መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡  ሁልጊዜም እንደምንለው በሰላማዊ መንገድ የመብት ጥያቄ ማቅረብ ወንጀል አይደለም፡፡  መንግሰት በሰላማዊ መንገድ መብታቸውን ከሚጠይቁ ዜጎች ጋር እልህ አይጋባ ፣ ህገ መንግስታዊ መብቶቻቸው ይከበሩ ፣ የመብት ጥሰት ድብደባ እና ግድያው ይቁም፡፡  ሕገ-መንግስታዊነት የታሰርንለት፣ ከሀገር የተሰደድንለት፣ ብዙ ዋጋ የከፈልንበትና አሁንም እየከፈልንበት ያለ ዐሳብ ነውና  በሀገሪቱ ህጋዊነት እንዲሰፍን ህይወታቸውን እስከመስጠት ድረስ ዋጋ ለከፈሉ ዜጎች ክብር እንሰጣለን፡፡ ለሕገ መንግስታዊ ስርዓት መስፈን ዜጎች የከፈሉት ዋጋ እጅግ ብዙ እና ከበቂ በላይ ነውና ተጨማሪ ሰብዓዊ ዋጋ መክፈል ሳያፈልገን ሕገ መንግስቱ እንዲከበር አንጠይቃለን፡፡

ሕገ-መንግስቱ ይከበር!  

Tuesday, December 8, 2015

ጋምቤላ: የፌደራሊዝሙ ክሽፈት ማሳያ?


በዘላለም ክብረት


ሐሙስ 20 – 01 – 2003፣ ጋምቤላ ከተማ፡

የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አዲሱን የስራ ዘመኑን የመጀመሪያውን የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ በማጽደቅ ያጠናቀቀ ሲሆን፤ በመዝጊያው ስነ ስርዓት ላይ በጊዜው የክልሉ ፕሬዝደንት የነበሩት ኡሞት ኡባንግ ባደረጉት ንግግር፡

‹‹ጋምቤላን ወደ ቀድሞው ክብሯ እንመልሳታለን፡፡ ያችን አኙዋዎች፣ ኑዌሮች፣ መዠንገሮች፣ ኦፖዎች፣ ኮሞዎችና ደገኞች አንድ ላይ በሕብረት የሚኖሩባትን - ጋምቤላ፡፡ ሁላችንም አፍሪካዊያኖች ነን፡፡ ጥላቻና ልዩነት ለማናችንም አይበጁንም…››

በማለት የሁሉንም ተሰብሳቢዎች ልብ የሚነካ ሃሳብ አቀረቡ፡፡ 156 መቀመጫዎች ያሉት የክልሉ ምክር ቤትም በጭብጨባ ተናጋ፡፡ ኡሞት ይሄን ታሪካዊ ንግግር ሲያደርጉ ከኡሞት ጎን የተቀመጡት የክልሉ ምክር ቤት አፈጉባኤ እንዲሁም የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አሽኔ አስቲን ተከትለው ስለ ልማትና መከባበር ተናግረው አሁንም አዳራሹን በሌላ ጭብጨባ አናጉት፡፡ ከሚያጨበጭቡት የምክር ቤት አባላት መካከል ቁመተ ሎጋው የ50 ዓመቱ ከአኙዋ ዞን የተወከሉት አቶ በኳች ማሞ ይገኙበታል፡፡ 

እሁድ፡ 06 – 07 – 2007፣ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ፡

የቀድሞው የክልሉ ምክር ቤት አፈጉባኤና የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል ሆኑት አቶ አሽኔ አስቲን በኬኒያ ናይሮቢ አኝዋ ሰርቫይቫል፣ Bread for All እና GRAIN በተባሉ ዓለማቀፍ ተቋማት የተዘጋጀውን ዓለማቀፍ የምግብ ኮንፈረንስ ላይ ለመሳተፍ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ከሌሎች አራት ግለሰቦች ጋር (የዓለም ባንኩን አስተርጓሚ ፓስተር ኡሞት አግዋን ጨምሮ) ተገኙ፡፡ ነገሮች እንዳሰቡት ሳይሆን ቀረና አምስቱም ግለሰቦች በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ተይዘው ወደ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ዘርፍ (ማዕከላዊ) ተወሰዱ፡፡

ከአንድ ቀን በኋ ሰኞ፣ 07 – 07 – 2007፡ 

‹ምርጫ 2007› ሊደረግ ስልሳ ሰባት ቀናት ይቀሩታል፡፡ ‹አፈ-መንግስቱ› ኢቢሲ ከኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ጋር በመሆን  ባወጣው የፖለቲካ ፓርቲዎች የቅስቀሳ የአየር ጊዜ መሰረት የዕለቱ (በቴሌቪዥን ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ዜና በኋላ) ተረኛ በጋምቤላ የኢሕአዴግ አጋር ፓርቲ በመሆን ክልሉን እያስተዳደረ ያለው የጋምቤላ ሕዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጋሕአዴን) ነው፡፡ ጋሕአዴን በዕለቱ እየቀሰቀሰበት የነበረው ጉዳይ የዲሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ጉዳይ ሲሆን፤ በዚሁም መሰረት የክልሉ ህዝብ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተመረጡ የፓርላማ አባላት በፌደራል እና በክልል ደረጃ እንደተወከለና የውክልና ዴሞክራሲም በክልሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደላቀ ደረጃ እንደደረሰ ጠቅሶ ይቀሰቅሳል፡፡ በቅስቀሳው መሃል ከሚታዩት ምስሎች መሃል ግን አንዱ ጉዳዩን ለሚያውቅ ሰው ወይ ያስቃል አለያም ያስደነግጣል፡፡ አስቂኙ/አሳዛኙ ጉዳይ በ2002 ምርጫ የክልሉ ምክር ቤት ካለው 250 መቀመጫዎች መካከል አንዱን የያዙት የአኙዋ ዞን ተወካዩ አቶ በኳች ማሞ በክልሉ ፓርላማ ውስጥ የድምፅ አሰጣጥ ስርዓት ላይ እጃቸውን ሲያወጡ መታየታቸው ነው፡፡ ምክንያቱም አቶ በኳች ማሞ በቀን 07 – 07 – ’07 ‹‹መቀመጫውን ሀሬና፣ ኤርትራ ካደረገው ራሱን የጋምቤላ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋህነን) ብሎ ከሚጠራ የሽብርተኛ ድርጅት ጋር ግንኙነት ፈጥረሃል፣ በሃላፊነትም እያገለገልክ ነው›› ተብለው በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ  አንቀፅ 7 (2) መሰረት ከ 20 ዓመት እስከ እድሜ ልክ ሊያስቀጣ የሚችል ክስ ቀርቦባቸው ያለመከሰስ መብታቸው እንኳን ሳይነሳ በእስር ላይ ይገኛሉና፡፡ በኳች ታስረዋል፡፡ ጋሕአዴን ደግሞ የውክልና ዴሞክራሲ መጎልበት ተምሳሌት አደርጎ ይቀሰቅስባቸዋል፡፡

ሰኞ፣ 17 – 09 - 2007፡ ጋምቤላ፣ ማጃንግ ዞን፡

በአስገራሚ ሁኔታ የቀድሞው የጋምቤላ ክልላዊ ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል አቶ አሽኔ አስቲን በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ዞን መንድሽ የምርጫ ክልል በተካሔደው የክልል ምክር ቤት ምርጫ  ጋሕአዴንን በመወከል ምርጫውን በማሸነፋቸው የምርጫ ክልሉ ምርጫ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ማቴዎስ ኤፍሬም የተፈረመ የተመራጭነት መታወቂያ የተዘጋጀላቸው ሲሆን ‹የተመራጩ ፊርማ› የሚለው ቦታ ላይ ግን ፊርማቸውን አላሳረፉም፡፡ 

ለምን? ምክንያቱም አቶ አሽኔ አስቲን ከመጋቢት 06 - 2007 ጀምሮ ‹‹መቀመጫውን ሀሬና፣ ኤርትራ ካደረገው ራሱን የጋምቤላ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋህነን) ብሎ ከሚጠራ የሽብርተኛ ድርጅት ጋር ግንኙነት ፈጥረሃል›› ተብለው በፀረ-ሽብርተኝነት አቆጁ መሰረት ተከሰው በእስር ላይ ስለሆኑ፡፡ እንግዲህ አቶ አሽኔ አስቲን ምርጫ የተወዳደሩትም ያሸነፉትም በሌሉበት ሲሆን፤ በመጨረሻም በሌሉበት የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት  ተመራጭ ስለመሆናቸው በኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ የተመራጭነት መታወቂያ ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡

***

ኡሞት ኡባንግ በ2002 ምርጫ አሸንፎ ስልጣን የያዘውን የጋምቤላ ምክር ቤት አራተኛ የስራ ዘመን በ2003 መጀመሪያ ላይ ሲከፍቱ አሽኔ አስቲን በአፈ ጉባኤነት ከጎናቸው የነበሩ ሲሆን በኳች ማሞ ደግሞ የምክር ቤት አባል ሁነው ከፊት ለፊታቸው ተቀምጠው ነበር፡፡ አምስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ኡሞት ኡባንግ ከክልሉ ፕሬዝደንትነታቸው ተነስተው በፌደራል ደረጃ ሚኒስትር ዲኤታ ሆነው ቢሾሙም የያዙትን ይዘው ከሀገር ኮበለሉ፣ የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት አፈ ጉባኤና የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል አሽኔ አስቲን በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ታስረው ይገኛሉ፣ የምክር ቤት አባሉ በኳች ማሞም እንዲሁ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

እውነት ይህ ሁሉ የሚሆነው ህግና ስርዓት ባለበት ሀገር ነው? ብሎ መጠየቅ እዚህ ጋር ተገቢ ነው፡፡ የጋምቤላ አበሳ ግን ከዚህም ይልቃል፡፡

1. ጋምቤላ

የኢፌዴሪ ሕገ - መንግስት በአንቀፅ 47 ካቋቋማቸው ዘጠኝ የክልል መስተዳደሮች አንዱ ነው፡፡ የሕዝብ ብዛቱ ትንሽ ከሚባሉ ክልሎች አንዱ ሲሆን (የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለስልጣን የሃምሌ 2007 ግመታ የክልሉ ሕዝብ ብዛት ሶስት መቶ ዘጠና ስድስት ሺህ እንደሆነ ያሳያል)፣ በአዲስ አበባ ከሚገኙት አስር ክፍለ ከተማዎች ውስጥ ‹በየካ ክፍለ ከተማ› ብቻ የሚኖረው ነዋሪ በአጠቃላይ በጋምቤላ ክልል ከሚኖረው ነዋሪ በእጅጉ ይበልጣል እንደ ማለት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር በጋምቤላ ክልል የሚኖረው ሕዝብ ከኢትዮጵያ ሕዝብ 0.4 በመቶውን ብቻ ይሸፍናል፡፡ (የሕዝብ ቁጥሩ ላይ የተለያዩ የክልሉ ልሂቃን ጥርጣሬ አላቸው) የሕዝብ ብዛቱ ከቆዳ ስፋቱ አንፃር ሲታይ ግን በኢትዮጵያ እንደ ጋምቤላ ህዝብ ሰፊ መሬት ላይ የሰፈረበት (sparsely populated) ክልል የለም፡፡ በንፅፅር ሲቀርብም ሃምሳ ከሚሆኑት የአውሮፓ ሀገራት ጋምቤላ አስራ ሶስት የሚሆኑትን በቆዳ ስፋት ይበልጣል፡፡ ጋምቤላ መሬቱ ሰፊ፣ የሕዝብ ብዛቱ ትንሽ እና እጅግ ለም ክልል ቢሆንም እንደ ጋምቤላ ጭቆናው፣ የመብት ጥሰቱ፣ ስደቱና መከራው የበዛበት ክልል የለም ማለት ደግሞ ስህተት ነው አያስብልም፡፡ 

በ1980ዎቹ አጋማሽ Cultural Survival በጋምቤላ የሚኖረውን የአኙዋ ዘውግ ‹አደጋ ላይ ያሉ ቡድኖች› ዝርዝር (endangered groups list) ውስጥ ካስገባው ጊዜ ጀምሮ ስለ ጋምቤላ ስቃይና መከራ እንደ Genocide Watch, Survival International, Oakland Institute, Inclusive Development, Human Rights Watch, Amnesty International, International Consortium of Investigative Journalists (ICIJ) የመሳሰሉ ፖሊሲ አፍላቂዎች (think tanks)፣ የመብት ተከራካሪዎች እንዲሁም ጋዜጠኞች ብዙ ሪፖርቶች፣ መግለጫዎችና ዘገባዎችን በተለያዩ ጊዜያት አውጥተዋል፡፡ የግጭት ተንታኞች (conflict analysts) የፌደራል ኢትዮጵያን የግጭት መንስኤና መፍትሄ ሲተነትኑ ከጋምቤላ የተሻለ ምሳሌ ሊያገኙ አልቻሉም፡፡ እዚህም እዛም ጋምቤላ ነው በምሳሌነት የሚቀርበው፡፡ ለምን ጋምቤላ?

2. ጋምቤላና: ‘የፌደሬሽኑ ፈተና’?

ኢትዮጵያ የዘውግ ፌደራሊዝምን (ethnic federalism) በሕገ መንግስት ደረጃ ተቀብላ ተግባራዊ ማድረግ በጀመረችበት ወቅት ሂደቱ ዘውግ ፌደራሊዝምን በሕግ ደረጃ ከከለከሉትና ዘውጌ ፖለቲካ ፓርቲዎችን በሕግ ደረጃ ከሚያግዱት ከአብዛኖቹ የአፍሪካ ሀገራት የተለየ (divergent) በመሆኑ ትችትና ውዳሴ ከተለያዩ አካላት ይቀርብለት ነበር፡፡ ተችዎች ይህ ለአፍሪካዊያን መጥፎ ምሳሌ (precedent) ነው በማለት ከፋፋይ ነው ሲሉ ሲያጣጥሉት፤ አወዳሾቹ ደግሞ አፍሪካ ከተዘፈቀችበት የግጭት አዙሪት ለመውጣት ጥሩ መፍትሔ ነው በማለት ሲያሞግሱት ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ዘውጌ ፌደራሊዝም ከሃያ ዓመታት በኋላ እንደ ተችዎቹ ሆነ ወይስ እንደ አወዳሾቱ የሚለው ኦዲቲንግ የዚህ ፅሁፍ ዓላማ ባለመሆኑ በዚህ ፅሁፍ ለማየት አልተሞከረም፡፡

‹የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም ብዙ ውይይት ሳይደረግበት ነው አሁን ባለው ደረጃ ሕገ መንግስታዊ የሆነው› የሚለው የምሁራን ትችት እንዳለ ሆኖ ዘጠኝ ክልሎችንና ሁለት የከተማ አስተዳደሮችን (ድሬዳዋን በኋላ ሕገ መንግስቱን እንኳን ማሻሻል ሳያስፈልገው በአዋጅ የከተማ አስተዳደር አድርጎ ተቀብሏታል) ይዞ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ይህ በዋነኛነት ዘውግን መሰረት ያደረገው ፌደራሊዝም ግን የግጭትና መንስኤ መሆን የጀመረው በተግባራዊነቱ ማግስት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፌደሬሽን ዋነኛ የግጭት መንስኤ የሆነባቸው ክልሎች ደግሞ አራቱ ብዙሃኑን የሚወክል ‹አውራ ዘውግ› (dominant ethnic group) የሌለባቸው ክልሎች ማለትም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል፣ በጋምቤላ ሕዝቦች ክልል እና በሀረሪ ሕዝብ ክልል ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት አራት ክልሎች ተፎካካሪ ዘውጎች (competing ethnic groups) ያሉባቸው በመሆናቸው የሃብትና የስልጣን ፉክክሩ ነገሮችን በቀላሉ ወደ ግጭት እንዲያመሩ ያደርጓቸዋል፡፡ እንግዲህ ጋምቤላም ከነዚህ አራት ክልሎች አንዱ ነው፡፡

2.1. ‘አኙዋ’  ከ‘ኑዌር’

በአሁኑ ወቅት ያሉት ሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች የፌደራሉን ሕገ መንግስት መሰረት በማድረግ (በአብዛኛው ከፌደራሉ ሕገ መንግስት ቃል በቃል የተቀዳ) ራሳቸው የክልል ሕገ መንግስት አላቸው፡፡ የጋምቤላ ሕዝቦች ክልልም የራሱ የሆነ ሕገ መንግስት አለው፡፡ የጋምቤላ ሕዝቦች ሕገ መንግስትን ከሌሎች ክልሎች ሕገ መንግስትም ሆነ ከፌደራሉ ሕገ መንግስት በተለየ ‹የክልሉ መስራች አባላት› (titular groups) የሚል ሀሳብ ማካተቱ ነው፡፡ በዚህም መሰረት የጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልል ሕገ መንግስት አንቀፅ 46 መሰረት የጋምቤላ ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መስራች ብሔር ብሔረሰቦች አምስት ሲሆኑ የአኙዋ ብሔረሰብ፣ የኑዌር ብሔረሰብ፣ የመዠንገር ብሔረሰብ፣ የኦፖና ኮሞ ብሔረሰቦች ናቸው፡፡ ከነዚህ መስራች ብሔረሰቦች› መካከል የአኙዋና የኑዌር ብሔረሰቦች በድምሩ ከዘጠና በመቶ በላይ የሚሆነውን የህዝብ ቁጥር ሲይዙ ከአጠቃላይ የክልሉ ነዋሪዎች መካከል ደግሞ እነዚህ ሁለት ብሔረሰቦች ከሁለት ሶስተኛ የሚልቀውን ይይዛሉ፡፡ በመሆኑም የጋምቤላ ሕዝቦች ክልል ዋነኛ እጣ ፋንታ የሚወሰነው በሁለቱ ‹መስራች ብሔረሰቦች› ተፎካካሪ (competing) ግንኙነት ነው ማለት ነው፡፡

የተለያዩ የክልሉን ፖለቲካ ያጠኑ ግለሰቦች/ተቋማት ጋምቤላን ሰላም ካሳጧት ችግሮች አንዱና ዋነኛው በውስጡ ያሉት ዘውጎች የዕርስ በርስ ፉክክርና ግጭት (inter-ethnic conflict) ነው፡፡ ይህ ግጭትም የሃብት፣ የመሬት እና የስልጣን ፍክክር ነው በማለት ያብራራሉ፡፡ የግጭቶቹ መንስኤ በአጭሩ ይሄ ነው ማለት ከባድ ነገር ቢሆንም በዋናነት ግን ግጭቱና ቁርሾው በአኙዋና ኑዌር ዘውጎች መካከል እንደሆነ ጥናት ያደረጉ ቡድኖች ይገልፃሉ፡፡ የአኙዋ ዘውግ ልሒቃን ጋምቤላ በታሪክ የአኙዋ ምድር እንደሆነች ሌሎች ዘውጎች ከአሁኗ ደቡብ ሱዳንና ከአጎራባች ክልሎች በተለያዩ ጊዜያት እንደመጡ በመግለፅ የጋምቤላ ሃብትና ስልጣን ለባለታሪኩ (historical right) እንደሚገባ በመግለፅ ይሟገታሉ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ አብዛኛው የዘውጉ አባላት በደቡብ ሱዳን የሚኖሩት የኑዌር ብሔረሰብ ልሂቃን ጋምቤላ የሁላችንም ናት ከሚል መነሻ “መጤ” የሚለው ስያሜ አይገባንም በማለት ሃሳባቸውን ያቀርባሉ፡፡ የፖለቲካል ሳይንስ ምሁሩ መድሃኔ ታደሰ በተለምዶ የአኙዋ -ኑዌር ግጭት በኑዌሮች ‹ተስፋፊነት›ና በአኙዋዎች ከመሬታቸው ጋር ባለ ጥብቅ ቁርኝት መካከል የተፈጠረ አለመጣጣም እንደሆነ ሲገልፁ ‹‹Traditionally, the Anuak- Nuer conflict can be explained by the incompatibility (antithesis) of the expansionist nature of the Nuer and the Anuaks’ strong emotional ties with their land›› በማለት ነው፡፡

ይህን የተፎካካሪ ዘውጎች ውዝግብ ለመፍታት ተወሰደው ርምጃ ጋምቤላን የኑዌር፣ የአኙዋና የማጃንግ ዞኖች ብሎ በዘውግ መስመር በሶስት ዞኖች መክፈል ነው፡፡ ይህ መፍትሔ የበለጡ የድንበር ጥያቄዎችንና ከመፍጠር ባለፈ፣ የክልሉን ስልጣን ለመያዝ የሚደረገውን ፍክክር የበለጠ አጡዞ የባሰ ችግር ከማምጣት ባለፈ ለጋምቤላ ሕመም መድሃኒት ሊሆናት አልቻለም፡፡

2.2. ‘መስራቾቹ’ ከ’መጤዎቹ

ፖለቲካል ዲሞግራፊ በአካዳሚያው ውስጥ እንደ ጥናት መስክ ተቆጥሮ መጠናት ከጀመረ ከአንድ አስርት ዓመት ብዙም አላለፈም፡፡ ሳይንሱ በዋናነት የሚያጠናው በአንድ ፖለቲካል-ኢኮኖሚ ውስጥ የሚኖሩ የተለያዩ ሰዎች (ወጣቶች፣ ሽማግሌዎች፣ ሴቶች፣ ወንዶች፣ ሕፃናት፣ አካል ጉዳተኞች ወዘተ)፣ የተለያዩ እምነቶች፣ የተለያዩ ዘውጎች ወዘተ በስልጣንና በሌሎች ፖለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ስለሚያሳድሩት ተፅዕኖ ነው፡፡

ስደት (migration) እና ሰፈራ (resettlement) የጋምቤላን ፖለቲካል ዲሞግራፊ በዋናነት ባለፉት ሰላሳ ዓመታት ውስጥ ቀያይረውታል፡፡ ከላይ ያየነው የአኝዋ-ኑዌር የሻከረ ግንኙነት በደቡብ ሱዳን ረዥም ጊዜ ያስቆጠረ ግጭት ምክንያት ወደ ጋምቤላ በተሰደዱ የኑዌር ዘውግ አባላት ምክንያት ነው በማለት ብዙ ሊቃውንት ይገልፃሉ፡፡ በ1980ዎቹ የSPLA ወታደሮች የያኔው ኢሉባቡር የአሁኑ ጋምቤላ ምድር በመግባት በተለያዩ ጊዜያት የአኙዋ ብሔር አባላትን እንደገደሉ የጊዜው ሪፖርቶች ያሳያሉ፡፡ የ SPLA ወታደሮች ወደ ጋምቤላ የመግባት አላማም ደቡብ ሱዳን ውስጥ በነበረው የነፃነት ትግል ምክንያት ከደቡብ ሱዳን ተሰደው ወደ ጋምቤላ የገቡ የኑዌር አባላትን በአካባቢው ካለ ጥቃት ለመከላከል የሚል ነበር፡፡ በአጠቃላይ ኑዌሮች ወደ ጋምቤላ በብዛት መግባት በጀመሩባቸው 1980ዎቹ ውስጥ የጋምቤላ ፖለቲካል ዲሞግራፊ መቀየር ጀመረ፡፡ ዛሬ ከክልሉ ነዋሪዎች (እንደ ኢትዮጵያ መንግስት ቆጠራ) መካከል ወደ ሃምሳ በመቶ የሚሆኑት ነዋሪዎች የኑዌር ዘውግ አባላት ናቸው፡፡

በሌላ በኩል ከሶቬት ሕብረት መንግስት የሰፈራ ፕሮግራም በመኮረጅ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ደርግ) መንግስት የ1977ቱን ድርቅና ረሃብ ተከትሎ 1.5 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያንን ከድርቅ ተጎጅ አካባቢዎች በማንሳት ወደ ምርታማ አካባቢዎች ለማስፈር ባወጣው እቅድ መሰረት በ1978 መጀመሪያ ጀምሮ ከሰሜናዊ የሃገሪቱ ክፍሎች (በተለይም ከወሎና ከትግራይ) አጋማሽ ላይ በድርቅ ከተጎዱ አካባቢዎች ፕሮፌሰር ገብሩ ታረቀ እንደሚሉት በኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማርምያና አቶ ለገሰ አስፋው ‹በግዴለሽነት› በተመረጡ ሰባት የሀገሪቱ አካባቢዎች ሰዎችን ማጓጓዝና ማስፈር ተጀመረ፡፡ ከነዚህ ሰባት የሰፈራ ቦታዎች አንዱና ዋነኛው ጋምቤላ ሲሆን በ1978 ብቻ እንደ ካልቸራል ሰርቫይቫል ሪፖርት 17,553 አባወራዎችና እማወራዎች የሰፈሩ ሲሆን ይሄም በግለሰብ ደረጃ ታማኝ ቁጥሮች ከ60,000 እስከ 70,000 ሰዎች እንደሚደርስ ሲገልፁ አንዳንዶች ደግሞ እስከ 150,000 ይደርሳል በማለት ቁጥሩን ከፍ ያደርጉታል፡፡ ይህ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ የጋምቤላን ዲሞግራፊ ሁነኛ በሆነ መንገድ ቀይሮታል፡፡ 

የጋምቤላ ‹መስራቾች - መጤዎች/ደገኞች› (titulars verses non-titulars)  ፖለቲካም የተጀመረው ከዚህ ጊዜ ወዲህ ነው፡፡ ምንም እንኳን የሰፋሪዎቹ ቁጥር በተለያዩ ምክንያቶች እጅግ የቀነሰ ቢሆንም ይህ ‹በደገኞች›ና ‹በመስራቾች› መካከል ያለ ግጭት በአብዛኛው በአኙዋና በማዣንግ ዞኖች ጎልቶ የሚታይ ሲሆን የ1996ቱን እልቂት ጨምሮ እጅግ በጣም የብዙ ዜጎችን ሕይወት የቀጠፉ ግጭቶችን ያስከተለና እስከ አሁን ድረስም የቀጠለ ዂነት ነው፡፡ ባንዳንድ የክልሉ አካባቢዎችም በተሿሚ ባለስልጣናት አስተባባሪነት ሳይቀር ችግሮችና ለዘር ማጥፋት የቀረቡ ድርጊቶች እየተፈፀሙ እንደሆነ የቅርብ ጊዜ የክልሉ ግጭቶች ምስክሮች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አሁን በኢትዮጵያ ያለውን ዘውግን በዋነኛነት መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝም ሲወጥን በመስራቾችና በመጤዎች መካከል ሊፈጠር የሚችልን ችግር የማይፈታና ስንኩል ሁኖ የተዘጋጀ ነው፡፡ ይሄን ስንኩልነት ዶ/ር አስናቀ ክፍሌ ‹Federalism and Ethnic Conflict in Ethiopia: A Comparative Study of the Somali and Benishangul-Gumuz Regions> ባሉት የዶክትሬት ማሟያ ፅሁፋቸው ላይ ‹‹The makers of the federal constitution did not foresee how the institutionalisation of ethnic federalism would affect relationships between titular and non-titular communities›› በማለት የፌደሬሽኑ አወቃቀር ያመጣው አንድ ችግር እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡

2.3. ጋምቤላ ከአዲስ አበባ

የጋምቤላ ብሔራዊ ክልል የ2008 10ኛው የብሔር ብሄረሰቦች ቀን ተረኛ አስተናጋጅ ተብሎ አምና ቤኒሻንጉል ላይ በተከበረው 9ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን ላይ ተመርጧል፡፡ እንግዲህ ጋምቤላ ሕዳር 29/2008 10ኛውን የብሔር ብሔረሰቦች በዓል ታከብራለች ማለት ነው፡፡ ይህ በዓል ከተከበረ ከአራት ቀን በኋላ ታህሳስ 03/2008 ደግሞ የአኙዋ ዘውግ አባላት  12ኛውን የአኙዋ ሕዝብ ላይ የተደረገው በነሱ አጠራር ‹የዘር ጭፍጨፋ› (genocide) አስበው ይውላሉ፡፡ 

ታሕሳስ 03/1996 ለጋምቤላ ታሪክ ክፉ ቀን ነበር፡፡ የግጭት ቀን፡፡ ግጭቱ በዋናነት በክልሉ ‹መስራች› ዘውጎች (በተለይም በአኝዋ ዘውግ አባላት) እና ከሌላ የኢትዮጵያ ክፍሎች መጥተው በአካባቢው በሰፈሩ ሰዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት በርካታ የአኙዋ ዘውግ አባላት የተገደሉበት ነው፡፡ የግጭቱ መንስኤ በተለያዩ አካላት የተለያዩ ምክንያቶች ቢሰጡትም ሁሉም ግን በክልሉ መስራች ዘውግ አኝዋና ከሌላ ክልሎች በመጡ ሰዎች መካከል ተጀምሮ የፌደራል መንግስቱ ጣልቃ በመግባት ግድያ እንደፈፀመ ይስማማሉ፡፡ በወቅቱ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ የነበሩት መለስ ዜናዊ ለሮይተርስ በሰጡት ቃል እስከ ሁለት መቶ የሚደርሱ ሰዎች እንደሞቱ የገለፁ ሲሆን፣ ኢሕአዴግ ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ በአዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚሽን ማለትም በአዋጅ ቁጥር 398/1996 የተቋቋመው ‹ታሕሳስ 3 ቀን በጋምቤላ ብሔራዊ ክልል የተከሰተውን ግጭት የሚያጣራ ኮሚሽን› ጉዳዩን በራሴ መንገድ አጣርቼ ሀምሳ ዘጠኝ ወንዶችና አንድ ሴት ብቻ ናቸው የተገደሉት፣ ነገር ግን የመንግስት ወታደሮች ከህግ አግባብ ውጭ በመሄድ ጉዳት አድርሰዋል› በማለት የችግሩን ዋነኛ ተዋናዮች ለመነካካት ሙከራ አድርጓል፡፡ ሒውማን ራይትስ ዎች በአካባቢው ጥልቅ ጥናት በማድረግ ‹Targeting the Anuak: Human Rights Violations and Crimes Against Humanity in Ethiopia’s Gambella Region› በሚል ርዕስ በ1997 ባወጣው ሪፖርት ደግሞ የሞቱት ሰዎች ብዛት 424 እንደሆኑ ገልጿል፡፡ የተለያዩ ነፃ ዓለማቀፍ ተቋማትም ከዚህ የሒውማን ራይትስ ዎች ሪፖርት ጋር ተመሳሳይ ቁጥር ያላቸውን ሪፖርቶች ነው በተለያዩ ጊዜ የሚያቀርቡት፡፡

እንግዲህ ታህሳስ 03 – 1996 ያለፉትን አስር ዓመታት የጋምቤላ ፖለቲካ የወሰነች ክፉ ቀን ነች፡፡ ከዛች ቀን ወዲህ የጋምቤላንና የአዲስ አበባውን የፌደራል መንግስት ግንኙነት ይህችን ቀን ሳይጠቅሱ መተንተንም ሆነ መነጋገር አይቻልም፡፡ ይህም የፌደራል መንግስቱንና የክልሎችን የአለቃና ምንዝር ግንኙነት እንድናይ ያደርገናል፡፡ 

የአሁኑ የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት በፀደቀበት ዓመት 1987 ዓ.ም አሜሪካዊቷ የሽግግር ፖለቲካ (transitional politics) ሊቅ ማሪና ኦታዌ በNortheast African Studies ጆርናል ላይ ‹The Ethiopian Transition: Democratization or New Authoritarianism?› በሚል ርዕስ ባሳተሙት ፅሁፋቸው ‹ኢሕአዴግ ዴሞክራሲና ፌደራሊዝምን ለነገሩ ብቻ ነው የሚያወራው፣ ዴሞክራሲንና ፌደራሊዝምን አያውቃቸውም› የሚል ሃሳብ በመሰንዘር የፌደሬሽኑን ትክክለኛነት ተጠራጥረው ፅፈው ነበር፡፡ ከሃያ ዓመታት በኋላም ይህ እውነት ተቀይሯል ብሎ ደፍሮ የሚናገር ማግኝት ከባድ ነው፡፡ ክልሎች የፌደራል መንግስቱ ‹ቅልቦች› ከመሆናቸውም ባለፈ የፖለቲካ ነፃነታቸው አሁንም አጠያያቂ ነው፡፡ ይህ የክልሎችና የፌደራል መንግስቱ የጎንዮሽ የተንጋደደ ግንኙነት (vertical asymmetry) ደግሞ ከጋምቤላ ክልል የበለጠ ጎልቶ የሚታይበት ክልል አለ ማለት አይቻልም፡፡

ኢሕአዴግ ስልጣን ከያዘ ከአለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ወዲህ ጋምቤላን ካስተዳደሩት (የሽግግሩን ጊዜ ጨምሮ) ስድስት ፕሬዚደንቶች መካከል የመጀመሪያው አግዋ አለሙ በሃምሌ 1984 እቤታቸው በወታደሮች የተገደሉ ሲሆን፣ አራቱ (ሶስቱ ኦኬሎዎችና ጋምቤላን ለረጅም ጊዜያት ያስተዳደሩት አቶ ኡሞት ኡባንግ) ከኢትዮጵያ ኮብልለው የወጡ ሲሆን ሁሉም የፌደራል መንግስቱ ጋምቤላን እንደ ‹እንጀራ ልጅ› በማየት በፈለገው ጊዜ የPDO (Peoples Democratic Organizations) ፕሮጀክቱን የሚያስፈፅምበት፣ የፈለገውን ፓርቲ/ግለሰብ/ዘውግ የሚነቅል - የሚተክልበት ክልል ነው በማለት፣ ክልሉ የስቃይና የመከራ ምሳሌ ነው እያሉ በተደጋጋሚ ሃሳበቸውን በተለያዩ ጊዜያት ገልፀዋል፡፡ ከቀድሞዎቹ ሁለት ፕሬዚደንቶች መካከል ሁለቱ (ኦኬሎ ኝጌሎና ኦኬሎ አኳይ) የኢትዮጵያን መንግስት ለሃይል ለማስወገድ ከሚሰሩ ሃይሎች ጋር እንደሚሰሩ አደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ታዲያ ያስተዳደሩት ሁሉ የተገደሉበትና የተሰደዱበት ክልል ከጋምቤላ ውጭ ማን አለ? 

2.4. ጋምቤላ ከIndia

በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2003 ዓመቱን ሙሉ እንደ የያኔው የኢትዮጵያ የግብርና እና የገጠር ልማት ሚኒስትር አቶ ተፈራ ደርበው ‹ቢዚ› የነበረ ሚኒስትር አልነበረም፡፡ አቶ ተፈራ የተለመደውን ባለ 20 አንቀፅ የመሬት ኪራይ ውል ስምምነት ከተለያዩ ዓለማት (በተለይም ከሕንድ) ከመጡ ባለሃብቶች እና ከሀገር ውስጥ ባለሃብቶች ጋር ሲፈራረሙ (ለምሳሌ ያክል እዚህእዚህ ይመልከቱ) ነው ዓመቱን ያሳለፉት፡፡ መሬቱ ደግሞ በዋነኛነት ጋምቤላ ክልል የሚገኝ ነው፡፡ 

የጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በክልሉ ሕገ መንግስት አንቀፅ 40/6 ላይ ‹‹የመሬት ባለቤትነት የሕዝብ መሆኑ እንደተጠበቀ ሁኖ የክልሉ መንግስት ለግል ባለሀብቶች በሕግ በሚወስነው ክፍያ በመሬት የመጠቀም መብታቸውን ያስከብርላቸዋል…›› ተብሎ በተደነገገው መሰረት ከክልሉ አጠቃላይ መሬት 42 በመቶውን (የኢትዮጵያ መንግስት በ2011 ለሂውማን ራይትስ ዎች በፃፈው ደብዳቤ ከክልሉ መሬት 36 በመቶውን ብቻ እንደሆነ ቢገልፅም) ‹ለግል ባለሀብቶች ያዘጋጀውት ነው› በማለት ለፌደራል መንግስቱ ‹ይሄን መሬት እኔን ሁነህ አስተዳድር-አከራይልኝ› በማለት  በ2001 አካባቢ የሰጠው ሲሆን፤ የፌደራል መንግስቱም በአቶ ተፈራ ደርበው አማካኝነት የተለመደውን ባለ ሃያ አንቀፅ ውል (ከ2058 እስከ 2061 ለሚደርሱ 50 ዓመታት) እየፈረመ (ይህ ፅሁፍ እስከተዘጋጀበት ሕዳር 2008 ድረስ) ለዘጠኝ የውጭና ለሶስት መቶ ሰማኒያ ሁለት/ሰማኒያ ዘጠኝ የግል ባለሃብቶች ሰጥቷል፡፡ ከነዚህ ኩባንያዎች መካከል እንደ Karituri (ካሪቱሪ በቅርቡ ለሽያጭ ጨረታ ቀርቧል), Ruchi Soya Saniti Agro Farm Enterprise (SAFE), BHO Agro Plc. Verdanta Harvest Plc የመሳሰሉት የሕንድ ኩባንያዎች የአንበሳውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡ እንግዲህ ይህ ነው ጋምቤላና ‹የመሬት ቅርምት› (land grab) ዓለማቀፍ ጩኸት ማዕከል ያደረጋት፡፡ 

ከክልሉ መሬት ግማሽ የሚሆነው (በሌላ አነጋገር የቤልጅየምን ግማሽ የሚያህል መሬት) ለግል ባለሃብት ሊሰጥ ተዘጋጅቷል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ወደ 45,000 የሚጠጉ የክልሉ ነዋሪዎች በሰፈራ (villagization) ስም ከቀያቸው ተነቅለዋል፡፡ የሰፈራው ዋነኛ ዓላማም ‹ክልሉን ለግል ባለሃብቶች በስጦታነት ለማዋል ነው› በማለት ዓለማቀፍ ተቋማት የኢትዮጵያን መንግስት እየወነጀሉ ይገኛሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የግል ባለሃብቶቹ ደን በማውደም የአካባቢውን ስነ-ምህዳር እያዛቡት ነው በሚል ተጨማሪ ውንጀላዎች ይቀርብባቸዋል፡፡ ባለሃብቶቹ ‹የCorporate Social Responsibility (CSR) መርሆቻችን ተግባራዊ እያደረግን ነው› ቢሉም፣ ፈቃድ ሰጭው የመንግስት አካልም ‹Environmental Impact Assessment (EIA) አድርጌ ነው ፈቃድ የምሰጠው› ቢልም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአካባቢው ማህበረሰብ ‹ይህ አውዳሚ ልማት (unwanted development) ነው› በማለት በባለሃብቶቹ ንብረት ላይ ጥቃት እያደረሰ ሲሆን የክልሉ መንግስትም ለፌደራል መንግስቱ ይህ የመሬት ቅሚያ እንዲቆም ጥያቄ ማቅረብ ጀምሯል፡፡ የፌደራል መንግስቱ ግን ጋምቤላ ‹የብሔር፣ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን› እንድታከብር ከመምረጥ ባለፈ ለጥያቄዎቹ ምላሽ እየሰጠ አይደለም፡፡

ጋምቤላ እንግዲህ በነዚህ አስጨናቂ ሁኔታዎች መካከል እየቆዘመ ነው፡፡ የእነዚህ ሁሉ ችግሮች ውጤት ደግሞ ክልሉን እጅግ ኋላ ቀር ያደረገው ሲሆን በሃገሪቱ ውስጥ ያሉ ዳታዎች እንደሚያመላክቱትም የጋምቤላ ክልል በውልደት መጠን (fertility rate) ከሀገሪቱ ከፍተኛውን ቁጥር እንደያዘ ሲገልፅ ከሚወለዱት ሕፃናት መካከልም ብዙዎቹ የሚሞቱበት (infant mortality rate) ክልል ጋምቤላ ነው፡፡ በኤችአይቪ/ኤድስ ተጠቂነትም እንደ ጋምቤላ የተጠቃ ክልል የለም፡፡ የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከመቶ የክልሉ ነዋሪዎች ስድስቱ በኤችአይቪ ተጠቂ ናቸው ፡፡ በእናቶች ሞት፣ በመሃይማን ቁጥር፣ በመሰረተ ልማት ወዘተ ጋምቤላ ከአጠቃላይ የሀገሪቱ ክልሎች ጭራ ላይ ነው የምናገኝው፡፡ 

መፍትሔውስ? የተለያዩ አካላት ለመንግስት፣ ለለጋሽ ሃገራት፣ በክልሉ ለሚገኙ ልሒቃን፣ ለአፍሪካ ሕብረት የመሳሰሉት የጋምቤላን ዘርፈ ብዙ ችግር ለመፍታት ይሆናሉ ያሏቸውን የተለያዩ ሃሳቦች በተለያዩ መንገዶች ያቀርባሉ፡፡ ነገር ግን ጋምቤላን በተለያዩ መንገዶች ጠፍረው ከያዟት ችግሮች ለማላቀቅ ይህ ነው የሚባል አንድ መፍትሔ ማቅረብ ከባድ ነው፡፡

3. ‹ኡሞትን አስራችሁ - ኡሞትን ፍቱልን›

በፈረንጆቹ 2005 ኖርዌይ የሚገኝው የኖቤል ኮሚቴ ‹ለኖቤል የሰላም ሽልማት› እጩ አድርጎ ካቀረባቸው ግለሰቦች/ቡድኖች መካከል የአሜሪካው Public International Law and Policy Group (PILPG) ይገኝበታል፡፡ ቡድኑ ለእጩነት የበቃው በሕግ ረገድ ለዓለም ሰላም ላበረከተው አስተዋፅኦ ነበር፡፡ ቡድኑ በ2005 ከሰራቸው ስራዎች መካከልም በዲሴምበር 2003 ጋምቤላ ውስጥ በአኝዋ ዘውግ አባላት ላይ በኢትዮጵያ መንግስት ለደረሰው በሰብዓዊነት ላይ ለተፈፀመ ወንጀል (Crimes Against Humanity) በሄግ ለሚገኝው ዓለማቀፉ የወንጀል ችሎት (International Criminal Court) ያቀረበው አቤቱታ ይገኝበታል፡፡ ባለ 26 ገፁ አቤቱታ የኢትዮጵያ መንግስት የፈፀማቸው ዓለማቀፍ ወንጀሎች በችሎቱ ተጣርተው የሚመለከታቸው አካላት እንዲጠየቁ የሚያሳስብ ነው፡፡ አቤቱታውን በጋራ በጁን 13, 2005 ፈርመው በጊዜው የፍርድ ቤቱ ዋና ዓቃቤ ሕግ ለነበሩት ለዝነኛው አርጀንቲናዊ ሉዊስ ሞሪንሆ ኦካምፖ ያስገቡት ደግሞ የAnuak Justice Council ሃላፊ አቶ ኦባንግ ሜቶ ናቸው፡፡

ይህ ከሆነ አስር ዓመታት ገደማ እየሆነ ሲሆን፤ የ2003ቱ ሁከትና ግድያ ሲፈፀም የክልሉ ፕሬዝደንት የነበሩትና ግድያውን በመቃወም የሚታወቁት ኖርዌጅያኑ አቶ ኦኬሎ አኳይ ዛሬ በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ግድያውን አስተባብረዋል የተባሉትና በጊዜው የክልሉ የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊ ነበሩት አቶ ኡሞት ኡባንግ ከሃገር ኮብልለው ማኒላ፣ ፊሊፒንስ ከትመዋል፡፡ አቤቱታውን ለፍርድ ቤቱ ያቀረቡት አቶ ኦባንግ ሜቶ በሌሉበት በሽብርተኝነት ክስ በኢትዮጵያ ፍርድ ቤት 15 ዓመት ተፈርዶባቸዋል፡፡ የአኝዋን መጎዳት ለዓለም ማህበረሰብ ሲያሳውቁ የነበሩት ፓስተር ኦሞት አግዋም በሽብርተኝነት ክስ ተጠርጥረው በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ 

ለግድያውና ለሁከቱ እስከ አሁን ድረስ የተጠየቀ አንድም አካል የለም፡፡ ለዚህም ነው የአኝዋ ልሂቃን ‹ኦሞት ኦባንግን አስራችሁ - ኦሞት አግዋን ፍቱልን› እያሉ የሚገኙት፡፡ ለዚህም ነው ‹በክልሉ ሰላምን ማምጣት ከተፈለገ የፍትህ መስፈን ቀዳሚ ነው› የሚለው ሃሳብን የሚሰነዝሩት፡፡ ለዚህም ነው ‹በክልሉ ውስጥ ግፍ የፈፀሙ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት ሳይጠየቁ ንፁሃንን በግፍ በሽብርተኝነት እየከሰሰሱ ማሰር የክልሉን ችግር ቢያባብሰው እንጅ ሊያሻሽለው አይችልም› እያሉ የሚገኙት፡፡ ፍትህ ነው መፍትሄው?

4. ሊብራሊዝም? 

በታሕሳስ 2007 አስራ አንደኛው በበዓሉ አክባሪዎች አጠራር ‹የአኙዋ ጭፍጨፋ› መታሰቢያ በሚከበርበት ወቅት በተለያዩ የደቡብ ሱዳን ድረገፆች በአኙዋና - ኑዌር ልሂቃን መካከል ሞቅ ያለ ክርክርና ውይይት ነበር፡፡ የክርክሩና ውይይቱ መነሻ ደግሞ ኑዌሩ ዶ/ር Chuol Kompuok ‹Dancing with a wolf: A Reflection on Gambella Politics› በሚል ርዕስ የፃፉት ፅሁፍ ነው፡፡ ዶክተሩ ጋምቤላ ሰላም ትሆን ዘንድ የአኙዋና ኑዌር ግንኙነት ሰላማዊ መሆን እንዳለበት ገልፀው በመፍትሔነት ያስቀመጡት ጉዳይም እያንዳንዱን ግለሰብ ከቡድኑ ነጥለን እንደ ግለሰብ በማየት ፖለቲካልና ሲቪል መብቱን ማክበር የሚል ሊብራሊዝምን የሚያጣቅስ መፍትሔ ነው፡፡ ዶክተሩ በየዋህነት አክለውም አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ለዚህ በመፍትሔ እንዲሰራ በመምከር ረጅሙን ፅሁፋቸውን ያጠናቅቃሉ፡፡ 

በተከታዮቹ ቀናት ግን ዶክተሩ ላቀረቡት ሃሳብ ከአኙዋ ልሂቃን ጠንካራና ተቃራኒ ሆኑ ምላሾችን ነበር ያስተናገዱት፡፡ (ከመልሶቹ በጥቂቱ እዚህእዚህ እና እዚህ ላይ ማየት ይችላሉ)፡፡ የአኙዋ ልሒቃን ያቀረቡት ሃሳብ ‹በአኙዋ ብሂል ግለሰቡ ከማህበረሰቡ ጋር የጠበቀ ግንኑነት (communal attachment) ያለው በመሆኑ ከማህበረሰቡ ነጥለን መፍትሔ ብናቀርብ አኙዋን እንጎዳዋለን› የሚል ነበር፡፡ እንዲያውም አንዱ መላሽ በብስጭት የአኙዋን መጉዳት ለዶክተሩ ሲያስረዱ፡ ‹‹For the time being it seems worst for Anwaa and excellent for Nuers, but it will come for Nuers the next day. Then no body survives at the end›› በማለት ነበር፡፡  

ዶ/ር Chuol Kompuok መሰረታዊ የሆነውን የሊብራል አስተምህሮ እንደመፍትሔ ሲያቀርቡ ከላይ እንዳየነው አሁን በኢትዮጵያ ያለው የዘውግ ፌደራሊዝም እንደ ጋምቤላ ያሉ ‹አውራ ዘውግ› የሌለባቸውን ክልሎች መፍትሔ የማይሰጥ መሆኑን ተረድተው ይመስላል፡፡ ታዲያ የፌደራል ስርዓቱ በዚህ ጉዳይ ላይ አርቆ አስተዋይነት የጎደለው (myopic) በሆነበት ሁኔታ ዶክተሩ ተሳስተዋል ማለት እንችል ይሆን?

5. ዴሞክራሲ! ዴሞክራሲ! አሁንም ዴሞክራሲ!

‹‹ፌደራሊዝም የአንድነት ሃይሎች (unionists) እና ተገንጣይ ሃይሎች (secessionists) አንድ ላይ እንዲኖሩ የሚያደርግ ስርዓት ነው›› የሚለው የፌደራሊዝም ትርጉም እንደኛ አይነት ሀገር ላይ በመርህ ደረጃ ለመጣው የፌደራል ስርዓት ተስማሚ ትርጉም ይመስላል፡፡ ይህ ሲባል ግን እውነተኛውን ፌደራሊዝምን መሰረት ያደረገ ጉዳይን ነው፡፡ ‹ዩጎዝላቪያን ያፈረሳት አሃዳዊ ስርዓት ሳይሆን የይስሙላ ፌደሬሽን (pseudo-federation) ነው› የሚለው ድምፅ በተደጋጋሚ ከተለያዩ ሃይሎች የሚሰማውም የይስሙላ ፌደሬሽን መዘዙ ብዙ እንደሆነ ለማስረዳት ነው፡፡ 

ፌደራሊስቱና ሶስተኛው የአሜሪካ ፕሬዝደንት የነበሩት ጀምስ ማዲሰን ስለ ፌደራል መንግስትና ክልሎች ግንኙነት ሲገልፁ ‹‹The Federal and State governments are in fact but different agents and trustees of the people, constituted with different powers, and designed for different purposes›› በማለት ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር የማዕከሉና እና የክልል መንግስታት ግንኙነት ‹የአለቃና - ምንዝር› የሚሆን ከሆነ ፌደሬሽኑ ፌደሬሽን አይደለም ማለት ነው፡፡ ትክክለኛ ፌደሬሽን እንዲዘረጋና የማዕከልና የክልል መንግስታት የጎንዮሽ እኩልነት (horizontal equality) እንዲመሰርቱ ደግሞ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የግድ ነው፡፡ ያለ ዴሞክራሲ ትክክለኛ የፌደራል ስርዓት ሊኖር እንደማይችል Brian Galligan ‘Comparative Federalism’ ባሉት ፅሁፋቸው ሲያስረዱ፡

Can there be genuine federalism without democracy? The answer is negative if we are talking about modern or republican form of federalism. Moreover, it is hard to envisage alternative non-democratic bases to federalism that would be sufficient to anchor both spheres of government. If this is the case, successful federalism requires robust democracy in which citizens share membership of two political communities and participate politically in both.

በማለት ነው፡፡ ሲጠቃለልም ፌደራሊዝም ያለዴሞክራሲያዊ ስርዓት የይስሙላ ከመሆን ባለፈ የሚፈታው አንዳች ነገር አይኖርም ማለት ነው፡፡ 

የጋምቤላን ጉዳይም ስንመለከት አብዛኞቹ ችግሮች የፌደራል መንግስቱ በጋምቤላ ሊጭነው ከፈለገው የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ የዘውግ ፌደራሊዝም ተነስተው፤ ኢሕአዴግ ለጋምቤላ በተለያዩ ጊዜያት የራሱን ፓርቲና የራሱን ግለሰቦች ሲሾም - ሲሽር የነበረበት ሂደት ጋር የሚያያዙ ናቸው፡፡ የጋምቤላ ልሒቃንም ‹‹የፌደራል መንግስቱ እንደፈለገ ኢ-ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ጣልቃ እየገባ ስለሚያውክ ነው የጋምቤላ አበሳ የበዛው፡፡ ክልሉን በዘውግ ደረጃ ከሶስት ከፍሎ፣ የጋምቤላን መሬት ለውጭ ባለሃብቶች እንደፈለገ እያከራየ፣ የፌደራል መንግስቱ ፖሊስና ወታደሮች በፈለጉት ጊዜ እየገቡና የፈለጉትን እየፈፀሙ፣ የፈለገውን ሰውና ፓርቲ ለክልሉ ከማዕከል እየሾመ ጋምቤላ ሰላም እንድትሆንና እድገት እንዲመጣ መመኝት ድካም ነው› በማለት በተለያየ ጊዜ ሃሳባቸውን ያቀርባሉ፡፡ እንዲያውም የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም ሊያጣጥም የሚገባውን የአንድነትና የተገንጣይ ሃይሎችን ፍላጎት ከመመለስ ይልቅ አዳዲስ ተገንጣይ ሃይሎች (secessionist movements) በማፍራት ዛሬ ጋምቤላን ከፌደሬሽኑ መገንጠልን እንደ ዓላማ በፕሮግራማቸው ይዘው የተነሱ ሃይሎችን ማየት ጀምረናል፡፡ ከላይ የጠቀስናቸው ዶ/ር አስናቀ ክፍሌ የኢትዮጵያ ፌደሬሽን ‹‹… has neither granted political autonomy nor ended secessionist wars›› ብለው የፌደራል ስርዓቱን ከተቹበት አገላለፅ ባለፈ፤ አሁን ያለው ፌደሬሽን አዳዲስ ተገንጣይ ሃይሎችን እየፈጠረም ነው ማለት ይቻላል፡፡ ‹ለዚህም መፍትሔው ዴሞክራሲያዊ ፌደራሊዝም ነው› የሚለው ሃሳብ የብዙ የዘርፉ ምሁራን ሃሳብ ነው፡፡

ከላይ ያሉት ትችቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች እንዳሉ ሆነው፤ እንደ አሽኔ አስቲንና በኳች ማሞ ያሉ የክልሉ የፓርላማ አባላት እንዲሁም እንደ ኦባንግ ሜቶና ኦሞት አግዋ ያሉ የክልሉ ልሒቃንን ‹በሽብርተኝነት› ወንጀል እየከሰሱ፤ እያሰሩና ረጃጅም ፍርድ እየፈረዱ ክልሉን ‹የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን› በዓልን አክብር ቢሉት ጭፈራውና ደስታው ከቴሌቪዥን ማሞቂያነት ባለፈ ምንስ ፋይዳ ይኖረዋል?

Friday, December 4, 2015

የነዘላለም ወርቅአገኘሁ መከላከያ ምስክርነት ሒደት

በእነዘላለም ወርቅአገኘሁ መዝግብ ተከሰው የነበሩት 4 የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አብርሃም ሰለሞን ነፃ ቢባሉም በይግባኝ ታግደው ፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት እየተመላለሱ እንደሆነ ይታወቃል። አሁንም ለቃል ክርክር ሕዳር 29, 2008 ተቀጥረዋል። ቀሪዎቹ፣ ማለትም ዘላለም ወ/አገኘሁ፣ ዮናታን ወልዴ፣ ባሕሩ ደጉ፣ ሰለሞን እና ተስፋዬ ከሕዳር 13–16, 2008 ድረስ ከፊል መከላከያዎቻቸውን ያስደመጡ ሲሆን ቀሪውን ዛሬ (ሕዳር 24, 2008) ያስደምጣሉ።
እነዘላለም ተከላከሉ የተባሉት በፀረ–ሽብር ሕጉ አንቀፅ 7/1 መሠረት የግንቦት 7 አባል በመሆን ሠርታችኋል በሚል ነው። በ5ቱም (ዘላለም፣ ዮናታን፣ ባሕሩ፣ ሰለሞን እና ነፃ ተብሎ በይግባኝ የተያዘው አብርሃም ሰለሞን) ላይ የመሰከሩት 3ተኛ የዐ/ሕግ ምስክር አቶ እዮብ ሲሆኑ፣ የምስክርነታቸው ጭብጥ በጥቅሉ ‘ዘላለም ወ/አገኘሁ መልምሏቸው ለግንቦት 7 ወታደርነት 3 ሰዎችን መልምለው ከወሰዱ በኋላ ጎንደር ላይ ባለመስማማታቸው እንደተመለሱ። ከ3ቱ አንዱ እዚሁ መዝገብ ላይ 8ኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ሰለሞን መሆናቸውን። አቶ ዘላለም በባሕሩ እና ዮናታን ሥር የተደራጀ ቡድን መኖሩን እንደነገሯቸው’ የሚያስረዳ ነው።
አቶ ሰለሞን፣ ዮናታን እና ዘላለም ከፊል ምስክሮቻቸውን ያስደመጡ ሲሆን አቶ ተስፋዬ (10ኛ ተከሳሽ) ጉዳያቸው ከነዘላለም የተለየ ቢሆንም አንድ መዝገብ በመሆናቸው ምስክሮቻቸውን አስደምጠው ጨርሰዋል።
አቶ ሰለሞን ሁለት ምስክሮችን አቅርበው እዮብ "የተሻለ ሥራ አገናኝሃለሁ በሚል አቶ ሰለሞንን ወደጎንደር ከወሰዷቸው በኋላ ጎንደር ሲደርሱ ለግንቦት ሰባት ወታደርነት እንደሆነ ሲነግሯቸው" መመለሳቸውን አስመስክረዋል። ራሰቸውም በሰጡት ቃል እዮብ እየወሰዳቸው እያለ መቶ አለቃ እያለ ከሚጠራው ሰው ጋር በስልክ ይነጋገር እንደነበርና የዘላለምን ስም ጨርሶ እንዳልሰሙ ተናግረዋል። 
ዮናታንም በበኩሉ እስካሁን 4 ምስክሮችን አስደምጧል። የመጀመሪያው አብሮ አደግ ጓደኛው ሲሆን፣ ዮናታን ውጭ አገር ለሚደረግ የሰብኣዊ መብትና ሚዲያ ነክ ሥልጠና ሊሄድ መሆኑን ነግሮት እርሱም ከፈለገ ሲቪውን እንዲሰጠው ጠይቆት መስማማቱን፣ ነገር ግን ሥልጠናው ባልታወቀ ምክንያት መስተጓጎሉን ለችሎቱ አስረድቷል። በሁለተኝነት የቀረበው ምስክር አቶ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ ስለእነዚህ ዓይነት ሥልጠናዎች ሠላማዊነት እና ሰጪዎቹም ዓለምዐቀፍ ዕውቅና የተቸራቸው ስለመሆኑ የባለሙያ ምስክርነቱን ሰጥቷል። በሦስተኝነት የቀረበው ምስክር አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ እዮብ ማዕከላዊ እያለ አናግሮት እንደነበር፣ ዮናታንን ፍፁም እንደማያውቀው፣ በኋላ ግን በድብደባ ብዛት እግሩ ተጎድቶ ማንከስ ሲጀምር እና ሥራ የሌላት ሚስቱና ልጁ ዕጣ ሲያሳስበው ተስፋ በመቁረጥ ሌሎቹ ላይ መስክሮ ሊፈታ መሆኑን እንደነገረው ለችሎቱ ነግሯል። በአራተኝነት ዘላለም ወ/አገኘሁ ቀርቦ እዮብ "ዘላለም በዮናታን ሥር ቡድን አለ ብሎ ነግሮኛል ያለው ሐሰት ነው" ብሏል።
ዘላለም ወርቅአገኘሁም ለራሱ እስካሁን 4 መከላከያ ምስክሮችን ያስደመጠ ሲሆን በቀዳሚነት የቀረበው ጥበቡ የተባለው አብሮ አደግ ጓደኛው ነበር። ጥበቡ፣ በክሱ ላይ የግንቦት 7 አመራር ተብሎ የተጠቀሰው ተድላ ደስታ አብሮ አደግ ጓደኛቸው እንደሆነና፣ እንግሊዝ አገር ከሄደ በኋላም ተማሩ እኔ ገንዘብ እልክላችኋለሁ ብሎ ገንዘብ ለሁለቱም እንደላከላቸውና ዘላለም ከመያዙ በፊት ማስተርሱን መማር እንደጀመረ ተናግሯል። የዘላለም እናት ወ/ሮ የኔእናትም በበኩላቸው ተድላ ደስታን ከልጅነቱ ጀምሮ የሚያውቁት የልጃቸው ጓደኛ በመሆኑ መሆኑን ጠቅሰው በ2005 ብር ልኮለት እሳቸው ጨምረውበት ዘላለም ትምህርት መጀመሩን ለችሎቱ ገልጸዋል። ቀሪዎቹ ሁለት ምስክሮች ሙዘሚል እና አዲሱ የተባሉ በክሱ ላይ በዘላለም ለግንቦት 7 የተመለመሉ እንደሆኑ የተገለጹ ወጣቶች ናቸው። ሁለቱም ወጣቶች በየተራ ከዘላለም ጋር ያላቸው ዕውቂያ በሰፈር ልጅነት እንደሆነና ምንም ዓይነት የሚያውቁት ቡድን እንደሌለ እና በቁም ነገር ቁጭ ብለው ያወሩበት አጀንዳም እንደሌለ ተናግረዋል።
ዘላለምና ዮናታን በሰጡት መከላከያ ቃላቸውም ላይ ወደውጪ ለሰብኣዊ መብትና ሚዲያ ነክ ሥልጠናዎች ለመሄድ ክሱ ላይ የግንቦት ሰባት አመራር ተብሎ የተጠቀሰው እና እነርሱ በጋዜጠኝነቱ እንደሚያውቁት የተናገሩት አርጋው አሽኔ ጋር ከመነጋገራቸው በቀር ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ተናግረዋል። ዘላለም፣ ሌሎችን ላለማስፈራራት ሲል ዝርዝሩን እንደማይናገር ነገር ግን በሐምሌ ወር፣ በቀዝቃዛ እና ዘጠና ሳንቲሜትር በሆነች ጨለማ ክፍል ውስጥ 41 ቀን መቆየቱንና ጠባሳ የማይተው ነገር ግን የነርቭን ስርዓት በሚያዛባ ምት እየተመታ መመርመሩን ተናግሯል።
በጥቅሉ ዐ/ሕግ ያቀረበው ክስ እና ማስረጃ ጠቅላላ ምስል፣ «ከውጭ አገር ገንዘብ በሚላክለት ዘላለም አማካኝነት የተመለመለው እዮብ ለግንቦት ሰባት ወታደሮችን እየላከ፣ ዘላለምም በሠላማዊ ትግል ሥም ቡድኖችን እያዋቀረ እንደሆነ» ለማሳየት ሲሞክር፣ እነዘላለምም በመከላከያቸው «ከውጭ አገር የተላከው ገንዘብ የዘላለም አብሮ አደግ ጓደኛ ለዘላለም የግል ፍላጎት የላከው መሆኑን፣ እዮብ ለግንቦት ሰባት ወታደርነት [እያታለለ] በወሰዳቸው ሰዎች ውስጥ ዘላለም እጁ እንደሌለበት፣ ቡድን እየተባለ የሚጠራ ነገር እንደሌለ እና ዜጎች ሁሉ ቢወስዱት የሚመከር ሥልጠና ለመውሰድ መጻጻፋቸውን በዚያ መንገድ እንደተተረጎመባቸው» የሚያስረዳ የመከላከያ ምስል ለመፍጠር እየሞከሩ ነው።

Thursday, November 19, 2015

ዛሬ 500 ቀናት በእስር የሚሞላው የወኅኒ ጓደኛዬ ትዝታ

በፍቃዱ ዘ ኃይሉ
‹‹…ይወስዳል መንገድ፣ ያመጣል መንገድ 
አንድ የሚጠላ፣ አንድ የሚወደድ…››

ሕይወት መንገድ ነች፡፡ በየመንገዱ ከሰው ታወዳጀናለች፤ ከተወዳጀናቸው ታለያየናለች፡፡ እኔም በሕይወቴ ጎዳና በገጠመኝ የእስር ሕይወቴ ካፈራኋቸው ወዳጆቼ ዘላለም ወርቅአገኘሁ አንዱ ነው፡፡ ሁሌ ‹‹ለምን ሳንታሰር አልተዋወቅንም?›› እንባባላለን፡፡ ቀድሞ መተዋወቁ የተለየ ነገር ይፈጥር ይመስል፡፡

ዘላለም ወርቅአገኘሁ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋለው ሐምሌ 1፣ 2006 ነበር፡፡ ልክ ከእኛ ውስጥ (ከአቤል በቀር) ወንዶቹ ሁሉ ‹‹ሳይቤሪያ›› ከሚባለው ቀዝቃዛ የምድር ክፍል ወጥተን ‹‹ሸራተን›› ወደሚባለው አንፃራዊ ምቹ ክፍል የተዘዋወርን ዕለት ማለት ነው፡፡ እኛ ወደ‹‹ሸራተን›› የተዛወርነው ለካስ እሱን ጨምሮ ለነሀብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ እንዲሁም ለነባሕሩ፣ ዮናታን፣ አብርሃም እና ሌሎችም ቦታ መልቀቅ ስላለብን ነበር፡፡ አንድም እንዳንቀላቀል፣ አንድም ምሥጢር እንዳንለዋወጥ መሆኑ ነው፡፡ ዘላለም ወርቅአገኘሁ የገባው፣ የኛው ዘላለም ክብረት ወደነበረበት 5 ቁጥር ነበር፡፡ እዚያ ግን ብዙ አልቆየም፡፡ ከዚያ ክፍል ወጥቶ ጭራሹኑ መብራት ወደሌለው እና ከአንድ ሰው በላይ በማያሳድረው ጭለማ ክፍል (ስምንት ቁጥር ) ውስጥ ገብቷል፡፡ ስምንት ቁጥር ውስጥ 41 ቀናት ቆይቷል፡፡

በጨለማ ቤት 24 ሰዓት፣ ለብቻ መቆየት ምን ያክል ከባድ እንደሆነ መገመት ይከብዳል፡፡ ለተወሰኑ ቀናት ከአብርሃ ደስታ ጋር ተጎራብተዋል፡፡ ከዚያ በፊት ባይተዋወቁም (ዘላለም በሥም ያውቀው ነበር) ግድግዳ እየደበደቡ ይነጋገሩና ማፅናኛ ቃላትም ይለዋወጡ እንደነበር ሁለቱም ነግረውኛል፡፡ ዘላለም ከታሰረ ዓመት ሲሞላው ‹‹በእስር ቆይታዬ የተረዳሁት የ24 ሰዓትን ርዝመት፣ የዓመትን እጥረት ነው›› አለኝ፡፡ ‹እንዴት?› አልኩት፤ ‹‹ስምንት ቁጥር እያለሁ 24 ሰዓት ማለት ፈፅሞ የማያልቅ ረዥም የጊዜ ዓይነት ነው፡፡ ዓመት ደግሞ በእስር ዓይን መለስ ብለህ ስትመለከተው በጣም አጭር ነው፡፡ አሁን ሳስበው የገባኝ የሁለቱ አያዎ (paradox) ነው›› አለኝ፡፡ እውነቱን ነው፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ‹‹በእስር ቤት አንዱ ቀን ከሌላኛው ቀን፣ አንዱ ሳምንት ከቀጣዩ ሳምንት፣ ወሩ ከሚቀጥለው ወር ጋር አንድ ዓይነት ናቸው›› ብለው ጽፈዋል፡፡ እውነት ነው፤ ስለዚህ መለስ ብለው ሲመለከቱት ዓመቱ በጣም አጭር ይመስላል፡፡ ዘላለም የተረዳው ያንኑ ነው፤ የጨለማ ቤቷን ተሞክሮ የገለፀልኝ ደግሞ እኔ ልገልፀው ስቸገር የነበረውን ነው፡፡

ዘላለም ወርቅአገኘሁ ካየኋቸው ክሶች ሁሉ የተንዛዛ ክስ ነው የተመሠረተበት፡፡ ክሱ ብቻውን ዘጠኝ ገጽ ነው፡፡ ፌስቡክ ላይ ያደረገው ቻት፤ ቤቱ የተገኙ የትምህርት እና ሌሎችም ጽሑፎች በሙሉ ክሱ ውስጥ ተተንትነዋል፡፡ ማስረጃ ተብለው ተያይዘዋል፡፡ ከተያያዙበት የሰነድ ማስረጃዎች መካከል ጥቂቶቹን ለትዝብታችሁ ያክል ልንገራችሁ፡፡

አንድ ገጽ ሙሉ በእስኪርቢቶ የተጻፈ ጽሑፍ ነው፤ እንዲህ ይነበባል፣
“If Blogging is a Crime,
then I am a Blogger too.
Free Zone9 Bloggers”

እንዳየሁት በጣም ነበር የደነገጥኩት፡፡ ብዙ ሰዎች በእጃቸው ‹‹መጦመር ወንጀል ከሆነ እኔም ጦማሪ ነኝ፤ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ይፈቱ›› የሚል ጽሑፍ ይዘው ፎቶ እየተነሱ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየለጠፉ እንደነበር ሰምቻለሁ፡፡ ነገር ግን የሽብር ክስ ማስረጃ ሰነድ ሆኖ ይመጣል ብዬ ግን ጠርጥሬ አላውቅም፡፡ ኢሕአዴግ ብዙ ጊዜ ያስገርመኛል (surprise ያደርገኛል)፡፡ በዚህም አስገረመኝ ከማለት ውጪ ቋንቋ የለኝም፡፡

ሌላም በጣም አስገራሚ ሰነድ ‹‹የሠራኸውን ወንጀል›› ያስረዳል ተብሎ ቀርቦበታል፡፡ ሰነዱ አንዳንዶች እንደሚሉት ‹‹ለኢሕአዴግ ብሉይ ኪዳኑ ነው››፡፡ ሰነዱ “On the Questions of Nationalities in Ethiopia” ይላል፡፡ የብሔር ጥያቄን በወረቀት ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ አቀንቅኗል የሚባልለት የዋለልኝ መኮንን መጣጥፍ ነው፡፡ ታዲያ የዚህ መጣጥፍ ገጽ ዘላለም ወርቅአገኘሁ ክስ ላይ ማስረጃ ሰነድ ተብሎ ተያይዟል፡፡ ይህንን ሰነድ ምን ብለው ያስተባብሉታል?

እነዚህም ብቻ አይደሉም፡፡ ዘላለም በታሰረበት ወቅት በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን ማስተርሱን በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ እያጠና ነበር፡፡ ታዲያ በወቅቱ ያገላብጣቸው የነበሩ ጥናቶችም ማስረጃ ተብለው ከክሱ ጋር ተያይዘው ቀርበውበታል፡፡ ለምሳሌ የሚከቱሉት ርዕሶች ያሏቸው ጽሑፎች አሉ፤ “Academic freedom” (የትምህርት/ማስተማር ነጻነት)፣ “University for Society” (ዩንቨርስቲ ለማኅበረሰብ)፣ እና “Social Service” (ማኅበራዊ አገልግሎት)፡፡ እንግዲህ እነዚህ በይፋ የሚታወቁ ትምህርት ነክ የሆኑ አጀንዳዎችን የሚታወቁ ጥናቶችን ማስረጃ ብሎ የሽብር ክስ ላይ ማያያዝ አንድም የከሳሾቹን አላዋቂነት ያሳብቃል፡፡ ያውቃሉ ቢባል እንኳ እያወቁ አጥፊነታቸውን ይናገራል፡፡ በተጨማሪም፣ የኔልሰን ማንዴላ ‘Long Walk To Freedom’ የተሰኘውና ከዋናው እትም አጥሮ የተጻፈው መጽሐፍ ገጽ 25 ላይ የሰፈረው፣ ኔልሰን ማንዴላ ‹የሕንድ ብሔራዊ ኮንግረስ›፣ ፓርቲያቸው ‹የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ› ለሚያደርገው ትግል አርኣያ እንደሆነው የሚያትቱበት ጽሑፋቸው ዘላለም ላይ ማስረጃ ተብሎ ተጠቅሶበታል፡፡

ዘላለም በዐቃቤ ሕግ ምስክር ሳይቀር የተነገረበት አንዱ ‹‹በሽብር ተፈርዶበት ውጪ አገር ከሚኖር የግንቦት 7 አመራር ገንዘብ ተልኮለታል›› የሚለው አንዱ ሲሆን፣ ይህንኑ ያስረዳል ተብሎ የተያያዘው ሰነድ ግን የሚያስረዳው ሌላ ነገር ነው፡፡ ሰነዱ የሚያስረዳው ተድላ ደስታ የተባለ ሰው ሦስት መቶ ዶላር እንደላከለት ነው፡፡ ተድላ ደስታ የ‹ደ ብርሃን› ጦማር ጸሐፊ ሲሆን፣ የግንቦት 7 አመራር ቀርቶ አባል ስለመሆኑ ምንም መረጃ ያልቀረበ ከመሆኑም በላይ ‹‹የተፈረደበት›› የሚለው ገሀድ ውሸት ነው፡፡

እንዲህ እና መሰል ክሶችን ታቅፎ የቆየው ዘላለም ነሐሴ 14/2007 ቀድሞ የተከፈተበት አንቀጽ 4 (ሲያንስ 15 ዓመት፣ ሲበዛ ሞት የሚያስቀጣ) ተቀይሮለት በአባልነት ብቻ፣ ማለትም 7/1 (ቢበዛ 10 ዓመት የሚያስቀጣ) አንቀጽ ተደርጎለት እንዲከላከል ተወስኖበታል፡፡ የዛኑ ዕለት በእሱ መዝገብ የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አብርሃም ሰለሞንም ‹‹ነጻ›› ተብለው ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ዐቃቤ ሕግ ይግባኝ በማለቱና የፍቺ እግድም ከጠቅላይ ፍ/ቤት በማሳዘዙ እስከዛሬ አልተፈቱም፡፡ ሌሎቹ የዘላለም ጓደኞች ባሕሩ እና ዮናታንም ቀድሞ በተከፈተባቸው አንቀጽ 7/1 እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል፡፡ የዘላለም ጓደኞች የተያዙት ከዘላለም ጋር በመሆን ወደውጭ አገር በመጓዝ የኢንተርኔት ደኅንነት ሥልጠና ሊወስዱ በተለዋወጡት ኢሜይል ሳቢያ እንደሆነ ይገመታል፡፡ ሥልጠናውን እያመቻቸላቸው የነበረው በስደት ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ አርጋው አሽኔ ሲሆን፣ አርጋው በክሱ መዝገብ ላይ ‹‹የግንቦት 7 አመራር›› ተብሎ ነው የተጠቀሰው፡፡ አርጋው አሽኔም እንደ ተድላ ደስታ ሁሉ እንኳን የግንቦት 7 አመራር ሊሆን አባል መሆኑንም የሚያስረዳ ማስረጃ የለም፡፡ ዛሬ ዘላለምና አራቱ ፖለቲከኞች በወኅኒ 500ኛ ቀናቸውን ያከብራሉ፡፡ ያከብራሉ ይባላል ወይ ብላችሁ እንዳትጠይቁኝ! ሌሎቹም በዘላለም ሥም በሚጠራው መዝገብ ላይ ያሉ የሕሊና እስረኞች ከሰሞኑ 500 ቀን ይሞላቸዋል፡፡

እኛ ስንያዝ የተረፉ (እና የተሰደዱ) ጓደኞቻችን ሰው ሊረዳላቸው ያልገባቸው ፈተና ውስጥ እንደነበሩ ሲያደርጉ ከነበሩት እና ሲልኩብን ከነበሩ መልዕክቶች ሰምተናል፣ ተረድተናል፡፡ ፈረንጆች ይህ ዓይነቱን ጉዳይ ‘survival’s guilt’ (‹የተራፊዎች የጥፋተኝነት ስሜት› እንበለው?) ይሉታል አሉ፡፡ ከዚያ ደግሞ ድንገት ክሳቸው ተቋርጦ የወጡት አባሪዎቻችን እኛን የከዱን ዓይነት ስሜት ይንፀባረቅባቸው ነበር፤ ይኸው ‹የተራፊዎች የጥፋተኝነት ስሜት› ሳይሆን አይቀርም፡፡ ቀሪዎቹም ተራችን ደረሰና ተንጠባጥበን ስንወጣ እኔ የጓደኞቼን ሕመም በከፊልም ቢሆን የተረዳሁት የመሰለኝ ዘላለምን ተሰናብቼ ስወጣ ነው፡፡

ዘላለም እስሬን ካቀለሉልኝ ሰዎች ውስጥ ዋነኛው ነው፡፡ ውይይታችን፣ ንትርካችን ሁሉ የማይዘነጋ ነበር፡፡ ማታ፣ ማታ መታጠቢያ ክፍሉ ውስጥ ካለች ጠባብ ኮሊደር ውስጥ የባጥ የቆጡን እየቀባጠርን እስከ ሌሊቱ ሰባትና ስምንት ሰዓት የምንቆይበት ጊዜ ነበር፡፡ በተለይ አምስቱ አባሪዎቼ ድንገት የወጡ ጊዜ የነበረውን የሐሳብ ውዥንብር እና የእንቅልፍ መዋዠቅ ከእሱ ጋር በማውራት ነበር ሰውነቴን ያላመድኩት፡፡ በእስር ቤት ቋንቋ ገበታ በጋራ የሚቋደሱ ሰዎች፣ መቅዱስ ነበር የሚባሉት፡፡ ዘላለም መቅዱሴ ብቻ አልነበረም፡፡ ወኅኒ የሰጠኝ ጓደኛዬም ነው፡፡ አሁን እቤቴ ቁጭ ብዬ አስበዋለሁ፡፡ ሳያመሽ መተኛት አይችልበትም፤ በጣም ያመሻል፡፡ ለቆጠራ 12፡30 በራችን ሲንኳኳ ‹ሀንጎቨር› እንዳለበት ሰው ዓይኑ ቅልትልት ብሎ፣ ፎጣ ደርቦ ሲወጣ ይታወሰኛል፡፡ ኳስ ጨዋታ ሲኖር (እኔ ባልወድም) ከጎረምሳው ሁሉ ጋር ሲሟገት ይታየኛል፡፡ ሰው መንከባከብ ይችልበታል፤ ሲንከባከበኝ ትዝ ይለኛል ልበል? አዎ፣ እንደሚንከባከበኝ ስለማውቅ እኔም እቀብጥ ነበር፤ እሱም ሲንከባከበኝ አስገራሚ ነው፡፡

ዘላለም ወርቅአገኘሁ እና ጓደኞቹ (5 ሆነው) የመጪው ሰኞ፣ ሕዳር 13፣ 2008 ራሳቸውን ለመከላከል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡ እኔም እንደተመልካች ላያቸው እሄዳለሁ፡፡ አልጨብጣቸውም፡፡ እጄን የማውለበልብላቸው ከሆነ እንኳን ፈራ ተባ እያልኩ ነው፡፡ እኔ ከትልቁ እስር ቤት ሆኜ፣ እነርሱ ደግሞ ከጠቧቧ ሁነው ያዩኛል፡፡ ‹ሁላችንም ነጻ ካልወጣን፣ አንዳችንም ነጻ ወጣን ማለት አይቻልምና!›

መልካም ዕድል ከመመኘት በላይ ምን አቅም አለኝ፡፡ መልካም ዕድል፣ የክፉ ቀን ጓዴ! መልካም ዕድል!
Zelalem Workagenegu drawing by Melody Sundberg


Wednesday, November 18, 2015

We are still prisoners!

Evidently six members of the Zone9 & three journalists are released from prison after they spent 14 to 18 months in prison. The three journalists and the two bloggers were released as the charges were ‘withdrawn’ in July. While the other four bloggers were acquitted in October. And one member the blogging collective, Befeqadu, was released on bail and he is yet to defend himself later this year in December on charges related with inciting violence.
However, since we walked free from prison we often are running into difficulties that suggest that we are not completely free and we can also testify that our difficulties are not easing off yet. As a result have decided to issue a brief statement on our situation:


      1.      The three journalists and the two bloggers who were released in July are still under travel restrictions although they got their seized passports back. For instance, Zelalem Kibret was denied exit and he got his passport confiscated at Bole International on November 15, 2015. He was traveling from Addis Ababa to Strasbourg, France to attend an award ceremony of Reporters Without Borders as Zone9 Bloggers are the recipient of the 2015 Citizen Journalism Award. Due to this complications Zelalem’s chance to travel to New York to attend CPJ Press Freedom Award ceremony is seriously hampered. We do not know why this happened to Zelalem but we want to remind that article 32 of the Ethiopian Constitution protects Ethiopians’ freedom of movement both within Ethiopia as well as to travel abroad.

     2.      The three bloggers, Abel Wabela, Atnaf Birahane, and Natnael Felek who were acquitted at the beginning of October have not got their seized passports and electronic equipment back. Although they have requested to have their confiscated passports and properties back stating the prosecutor’s ‘appeal’ as a reason, the concerned government agency denied them to get their properties back. But the issue of appeal is still unresolved and four weeks after their release the bloggers are yet to learn their fate

     3.      Abel Wabela, Edom Kassaye ,Mahlet Fantahun and Zelalem Kibret  were employees before their imprisonment. But so far their employers are not willing to rehire them or allow them back to their work. The time they spent in a prison is considered is as the fault of the bloggers and they are being laid off.


     4.      Recently, BBC reported that Prime Minister Hailemariam Desalegn insisted that we not real journalists and we had terror links. Likewise, other government officials also routinely give similar unconstitutional opinions which infringes the court’s pronouncement of our innocence.

Leaving these issues unattended is making us to feel as if we are living under a house arrest. The uncertainty coupled with and other issues putting us in an incredible amount of pressure to censor ourselves. Hence, we request the Ethiopian government or the concerned government agency  
1.      To respect our freedom of movement
2.      To return our seized properties and confiscated passports back
3.      To respect the court’s pronouncement of our innocence.



Respect the Constitution


Zone9 Bloggers & Journalists 

አሁንም እስረኞች ነን - ከዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች የተሰጠ መግለጫ

ከሚያዝያ 17 2006 ጀምሮ በፓሊስ ቁጥጥር ስርውለን የነበርነው 3 ጋዜጠኞችና እና 6 የዞን9 ጦማርያን ከአንድአመት ከሁለት ወር እና ከአንድ አመት ከ5 ወር የእስር ቆይታ በኋላ ሁላችንም ከእስር አንደተፈታን ይታወሳል፡፡ በሃምሌ ወር መጀመሪያሶስት ጋዜጠኞች እና ሁለት ጦማርያን አቃቤ ህግ ክስ አቋርጦ፣ በማስከተል አራት ጦማርያን ደግሞ ነጻ ተብለው ከእስር መለቀቃችንየሚታወስ ሲሆን ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ በዋስትና ላይ ሆኖ የቀረበበትን “አመጽ የማነሳሳት ክስ” እንዲከላከል መባሉም ይታወቃል፡፡
ይሁን አንጂ የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ከተፈታን ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ ነጻ አለመውጣታችንን የሚያሳዩ ተደጋጋሚ ተግዳሮቶች በመኖራቸውእና ሊቀየሩም ባለመቻላቸው ይህንን መግለጫ ለማውጣት ተገደናል፡፡
1.     የኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀጽ32 በሚደነግገው መሰረት “ ማንኛውም ኢትዮጲያዊ … በፈለገው ጊዜ ከአገር መውጣት ነጻነትን” በሚጻረር መልኩ “የመንቀሳቀስ መብታችን”አሁንም ተገድቧል፡፡ ለምሳሌ ጦማሪ ዘላለም ክብረት ህዳር 7/2008 በፈረንሳይ አገር በሪፓርተርስ ሳንስ ፍሮንቲየርስ (ድንበርየለሽ ጋዜጠኞች ድርጅት) ለዞን 9 ጦማር የተበረከተውን 2015 የሲቲዝንጆርናሊዝም ሽልማት የዞን9 ጦማርን ወክሎ ለመገኘት ህዳር 6/2008 ቦሌ አየር ማረፊያ ቢገኝም ባልታወቀ ምክንያት ከአገር መውጣት ተከልክሎ ፓስፓርቱንምተቀምቷል፡፡ በዚህም የተነሳ የሚቀጥለው ሳምንት በሚከናወነው በአለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከላካይ የሆነ የሲፒጄ የፕሬስ ነጻነት ሽልማት ላይ መገኘቱን እድልም በጣም አጥብቦታል ፡፡
2.    ጦማሪ አቤል ዋበላ (የኢትዮጵያአየር መንገድ ኢንጂነር) ፣ ጦማሪ ዘላለም ክብረት (የአምቦ ዩኒቨርሲቲ የህግ መምህር) ጦማሪት ማህሌት ፋንታሁን( የጤና ጥበቃሚኒስትር የዳታ ኦፌሰር) እና ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ (በፕላን ኢንተርናሽናል የኮምኒኬሽን እና ኖውሌጅ ማኔጅመንት ሰራተኛ) ወደስራገበታችን መመለስ አልቻልንም ፡፡ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ በሆነው መንገድ ተገደን ከአንድ አመት በላይ እስር ቤት መቆየታችን የእኛ ጥፋትአንደሆነ ተቆጥሮ ከስራ ተባረናል ፡፡ሌሎቻችንም በግል እንሰራቸው የነበሩ ስራዎችንም መቀጠል አልቻልንም ፡፡
3.    ከፍተኛው ፍርድ ቤት ከክሳችሁሙሉ ለሙሉ ነጻ ወጥታችኋል ብሎ የበየነልን ሶስት ጦማርያን ስንያዝ “ማአከላዊ” ምርመራ የተወሰደብን ፓስፓርታችን እና ሌሎች እቃዎቻችንእንዲመለሱልን ብንጠይቅም “ አቃቤ ህግ ይግባኝ ጠይቆባችኋል” በሚል ሰበብ እስካሁን አልተመለሱልንም፡፡
4.    ቢቢሲ አንደዘገበው የኢፌዴሪጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ አሁንም “ ታስረው የነበሩት ጋዜጠኞች እና ጦማርያን የእውነት ጋዜጠኞች አይደሉም ከሽብርጋር ግንኙነት አላቸው” በማለታቸው እንዲሁም የተለያዬ የመንግስት ባለስልጣናት የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ የሚሰጡት አስተያየት ፍርድቤቱ ያወጀልንን ነጻነታችንን ኢ- ህገመንግስታዊ በሆነ መንገድ እየናደው ነው ፡፡
በእነዚህእና በሌሎች ጫናዎች ምክንያት ራሳችንን ሳንሱር አንድናደርግ እና ሁሉም ጉዳያችን በእንጥልጥል ላይ ያለ የቁም እስረኞች የሆንንእንዲመስለን እየተደረገ ነው ፡፡ ስለሆነም
-      ህግ መንግስታዊ መብታችን የሆነውእና ምንም ህጋዊ ገደብ ያልተቀመጠበት በነጻነት የመንቀሳቀስ መብት መብታችን እንዲመለስልን
-      በኢግዚቢት ስም በማእከላዊምርምራ የሚገኙት እና ካለምንም ህጋዊ ምክንያት የተያዙት ፓስፓርት እና ሌሎች የግል እቃዎቻችን እንዲመለሱልን
-      መንግሰት የራሱን ፍርድ ቤትውሳኔ አክብሮ አሁንም ወንጀለኛ ስያሜ የሚሰጠንን ስም ማጥፋት እና የእጅ አዙር ጫና አንዲያቆምልን
-      የፓለቲካ ታማኝነትን ለማሳየትያለህግ አግባብ ወደስራ ገበታችን አንዳንመለስ ያደረጉን አካላት ውሳኔያቸውን መለስ ብለው እንዲያዩልን እንጠይቃለን፡፡

ሕገ መንግስቱ ይከበር
ዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን Citizen journalists of the year አሸናፊ ሆኑ

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን Reporters sans frontières / Reporters Without Borders / RSF በየአመቱ በሚያዘጋጀው የሽልማት ውድድር የዞን ዘጠኝ ጦማርያን Citizen journalists of the year አሸናፊ ሆኑ በትላንትናው ዕለት በፈረንሳይ ስትራስበርግ በተካሄደው ሥነ-ስርዓት የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ በማለት የሶሪያዋን ዜይና ኤርሃምን የሸለመ ሲሆን በዜጋ ጋዜጠኝነት ደግሞ የዞን ዘጠኝ ጦማርያንን ሸልሟል እንዲሁም የዓመቱ ሚድየም በሚል የቱርኩ Cumhuriyet Gazetesi አሸናፊ ሆኗል፡፡
ጦመርያኑ ጋር ከኩባ ፣ ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ኢራን፣ ሲንጋፖር፣ ቻይና እና ቬትናም ከሚገኙት ጋር ተወዳድረው ነው አሸናፊ ሆነው የተመረጡት፡፡
የዞን ዘጠኝ ጦማርያንን በመወከል ዘላለም ክብረት በቦታው ለመገኘት ያደረገው ጥረት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በመንግስት እንዳይወጣ በመደረጉ ምክንያት ሳይሳተፍ ቀርቷል፡፡
ዘላለም በፍትሕ ሚኒስቴር በሐምሌ መጀመሪያ ክሳቸው ተቋርጦ በነጻ ከእስር ከተለቀቁት ጦማርያን አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡

© Claude Truong-Ngoc 

ዘላለም ክብረት



Monday, November 16, 2015

“Terrorist” for being a ‘bachelor’!

BefeQadu Z.Hailu
Edited By:Endalk H. Chala
Aduňa Kesso is a Qeerroo. According to Aduňa, Qeerroo in Afan Oromo means ‘a young; bachelor who  who does not have a child yet’. “You can’t help it I’m a Qeerroo”, he jokes comparing the fact that I’m 10 years older than him. He was a 2nd year Electrical Engineering student at Adama University when he was arrested in May 2014.

Aduňa was arrested following students’ protest against the introduction of the controversial Addis Ababa’s new master plan. As the new master plan intends to integrate the sprawling capital, Addis Ababa with Oromia, the adjacent Regional State, the Ethiopian government calls it Addis Ababa-Oromia integrated Master Plan. But students particularly from Oromia consider the new master plan as Ethiopia’s central government illegal expansion into Oromia Regional State at the expense of local farmers. By then, I along with six of my colleagues from Zone9 and the three journalists were also in jail. During the heyday of university students protest. We were detained in Maekelawi, the country’s notorious pre-trial detention center and I have no idea of what was going on in the country. Maekelawi is not only a detention center but it also is a seclusion center. Twenty or so days into my 544 days of incarceration, we were joined by students from Oromia who were arrested due to their protest of the new master plan. In Maekelawi our cells were located in its infamous part,inmates call those cells ‘Siberia’ because of their unbearable cold. The new inmates were added to our tiny cells. Total of 15 students were arrested (11 of them were released from Maekelawi in political intervention from the Oromia state; 6students including two other students who were later detained and were charged of detonating a bomb at Haromaya University.Among them was Aduňa who became one of my inmates.

Aduňa is from Salaale,a rural part of Oromia. He is not only the first of his family members to have joined a university but also to a bit of have an exposure to urban life. In Adama University, he said, he learned about the ethnic issues of the country.He speaks little Amharic, the official working language of Ethiopia’s federal government. His interaction with non Afan Oromo speakers was limited and most of his friends were Afan Oromo speakers. He later had joined and became active member of the Oromo Students Association. It was in this process that Aduňa came to be interested in political activism. He joined Qeerroo Bilisumma Oromia (‘The Oromo National Youth Movement for Freedom and Democracy’), a lose network of Oromo youths for freedom and democracy. This has introduced him with other members of the network in different universities of Ethiopia.

As a part of his political activism, Aduňa has also joined social media - specifically Facebook.He has written his comments on wide range of issues. He spread news. I guess this might have instigated Ethiopia’s government Intelligence Office to tap his phone. Initially, Aduňa did not know that his phone was tapped; he learned about this when the prosecutor attached the paraphrased transcripts of his phone conversations as evidence to support government’s terrorism charges. The charges pressed against him were being a member of OLF an irrelevant political organization which is labeled as ‘terrorist group by the parliament of Ethiopian government. He was also charged in conspiring to detonate the bomb at Haromaya University, which caused a death of one student and 70 casualties.

When Aduňa was brought to Maekelawi his healing wounds on his arms and legs were visible. He told me that his wounds are from the tortures he received in anonymous locations. He had a punch blot on his face, under his left eye. But, he looked OK.To my surprise he jokes and laughs. For me, that was the time I was trying hard to get used to the first days of my rough experience. My first laugh came after his jokes; a laugh that made me feel I owe him the exact kind of laugh that you need when you think you won’t laugh again.

Before they moved him to Maekelwi, Aduňa spend 19 days in a place where he didn’t know because he was blindfolded when they arrested him and brought him to Maekelawi. He was beaten badly. His wounds on his legs are from kneel walks. He told me he was forced to kneel-walk on a concrete floor while being interrogated. Once, he told me, the interrogator was speaking on the phone with a woman while interrogating him. Aduňa had noticed the woman was making his interrogator laugh.This was, by experience, a good sign for Aduňa. “When he smiles,” Aduňa said,“The punishment usually eases”. So, he took advantage of this and stopped kneel walking while the interrogator was talking to the woman. Its consequence could be dangerous but Aduňa had to take a risk to get some relief from the pain of the interrogation hoping that the woman, at the other end of the phone, would make him laugh even more.  Once the interrogator ended his phone conversation with the woman and asked him, “Why did you stopped kneel walking?” Aduňa answered, “Ayi… Antaeskiticheris biyé naw” (No….I am just waiting until you to finish your phone call). Luck was with him, the interrogator laughed it off and allowed himto be interrogated while sitting. This is a brutal lived experience for Aduňa;but, he narrated it without any sense of resentment. His positive interpretation of things coupled with his limited but humorous Amharic was our source of vitality in Maekelawi. For Aduňa, ‘Siberia’ is like a haven when he compared it to the anonymous place where he was held immediately after his arrest. He used to say that “he had felt released when he was brought to Maekelawi.

A couple of days before his arrest, Aduňa received a call from his friend who was a student at Haromaya University. On the phone, Aduňa’s friend told him that an undefined people detonated a bomb while students were gathered to watch a soccer game in campus.Shocked with this irresponsible act of violence Aduňa reacted angrily on his phone “how could one do such a thing?” During his trial, Aduňa learnt that this part of his phone conversation was transcribed, paraphrased and used out of context as evidence to support government’s allegation of his terrorist activities. Infact Aduňa condemned the action and expressed sympathy for the victims;however, the police used it against him. Police claimed a connection only because his Qeerroo friends informed him about the tragic incident. However, for Ethiopian government giving a constructive feedback on their policies is counted a crime. Aduňa and his friends were just giving aconstructive feedback that the new master plan must not be implemented but, the government used the isolated tragic incident as an opportunity to destabilize their dissents.

Aduňa is not alone.There are many students whom I met in Maekelawi. Magarissaa Worku is one of them. Magarissaa was also senior studying law at Haromaya University when he was arrested in 2014. He went through the same ordeal as Aduňa did. (I will be back with other notes about Magarissa.)


Aduňa Kesso
After two months, I along with my fellow Zone9ners and the journalists were moved to Qilinto prison. The students who were arrested for protesting the new master plan were also brought to Qilinto prison. I met Aduňa again in Qilinto.  But, in Qilinto, Aduňa was not as
cheerful as he used to be in Maekelawi. They broke him. I always read solemnity on his face. We chatted a few times. He is helplessly angry. They destroyed his innocence. He told me that he is unhappy because staying in a prison with criminals could not make him happy.  He is right. For a person like him, for a person who shouted for a cause being imprisoned with criminals is sad. Even Maekelawi was better. It gives hope. In Maekelawi, most prisoners are political prisoners; and, they make you feel you are part of a struggle; you see the big picture. In Qilinto, it is different.You will be consumed inside the ocean of criminals. You will be no one!

Sunday, November 1, 2015

የተዘለለው ምዕራፍ

 በበፍቃዱ ዘ ኃይሉ
የሰለሞን ስዩምን ‹‹የኦሮሞ ጉዳይ እና የኢትዮጵያ ብያኔ›› የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ (ሁለተኛ እትም) አነበብኩት፡፡ በጥቅሉ ወድጄዋለሁ፡፡ ጥቂት ቅሬታዎች ግን አሉኝ፡፡ ሰለሞን በአማርኛ የኦሮሞ ጉዳይን ከጻፉ (እና እኔ ካነበብኩላቸው) ጸሐፍት ሁሉ በተሻለ ልለው በምደፍረው ደረጃ ምሁራዊ ታማኝነት (intellectual honesty) ተስተውሎበታል፡፡ አልፎ፣ አልፎ ግን ምሁራዊ ታማኝነቱ ከሚጎድላቸው ምሁራን ማጣቀሱ ሚዛን አስቶ ያንገዳገደው ይመስለኛል፡፡ ለምሳሌ የታቦር ዋሚ ‹‹የውገና ድርሰቶችና የታሪክ እውነቶች››ን ማንሳት ይቻላል፡፡ ታቦር ትልቅ ርዕስ ይዞ ትንንሽ ክርክር የተከራከረባቸው ቦታዎች አሉ፡፡ አንዱ የቋንቋ ተናጋሪዎች ብዛትን በተመለከተ የሚሰጠው ምንጭ አልባ ድምዳሜ ነው፡፡ ሰለሞን ያንን በኦሮሞ ጉዳይ ላይ ያንፀባርቀዋል፡፡ ‹‹. . . መረጃዎች አሉ›› በሚል ብቻ፡፡ በተጨማሪም አጠራጣሪ (አከራካሪ) ሁኔታዎች ላይ እምነቱን ለዘውግ ብሄርተኞቹ ትርክት ወደመስጠቱ አዘንብሎብኛል፡፡

ይህ በእንዲህ አያለ፣ መጽሐፉን አንብቤ ስጨርስ የጎደለ ነገር ያለ-ያለ ተሰማኝ፡፡ ታዲያ የጎደለ የመሰለኝን ምዕራፍ ለምን አልጽፈውም አልኩና ተነሳሁ፡፡ ጽሑፉን የምጽፈው የሰለሞንን ሐሳብ እየተዋስኩ፣ የኔን እየጨመርኩበት ነው፡፡ እሱም ይጭንብኛል፤ እኔም እጭንበታለሁ፡፡ ስለዚህ ከታች የማሰፍረው ጽሑፍ ላይ ‹እኔ›› እኔ አይደለሁም፡፡ ሰለሞን ስዩም ነው፡፡ እኔ ሁን እንዳልኩት፡፡

የተጣመመው የብሔርተኝነት ቅርንጫፍ
በኢትዮጵያ ቀኝ ዘመሞች አና ግራ ዘመሞች ሁሌም እርስ በርስ እንደተዋቀሱ ነው፡፡ እነዚህ ‹‹ትምክህተኛ ብሔርተኞች ፍፁም አሀዳዊ አገር ለመፍጠር ሊፍጨረጨሩ አገሪቱን ይበታትኗታል፡፡ ሲሉ፣ እነዚያ ‹‹ጠባብ ብሔርተኞች ሁሉንም ነገር በዘውግ ዓይን እያዩ አገሪቱን ሊበጣጥሷት ነው›› ይላሉ፡፡ መጽሐፉ በኦሮሞ ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡ ስለሆነም አሁን ማተኮር የምፈልገው የዘውግ ብሔርተኞች የሚከሰሱባቸው ችግሮች እና መፍትሔዎች ላይ ነው፡፡

አማራ-ሰግነት (Amhara Phobia)
ኦሮሞ ብሔርተኝነት ከገጠሙት ፈተናዎች መካከል አንዱ የኦሮሞ-ሰግነት እንደሆነ የሆነ ቦታ ገልጫለሁ፡፡ የአማራ ልሒቃን ያለውን ስርዓት ለማንበር ከመፈለግ ይሁን የኦሮሞ ልሒቃን ወደ ሥልጣን ከመጡ የቀድሞ የአማራ ገዢዎች በአባቶቻችን ላይ አድርሰውታል ለሚሉት በደል ‹ይበቀሉናል› በሚል ፍራቻ ኦሮሞ-ሰግነት ልንለው የምንችለው የኦሮሞ ብሔርተኝነትን የመፍራት ሥነ ልቦና አዳብረዋል፡፡ የይስሃቅ ኒውተን ሦስተኛ ሕግ በዚህም ይፈፀም ዘንድ፣ የአማራ ልሒቃን የአፀፋ ፍራቻ በኦሮሞ ልሒቃንም ዘንድ እየተንፀባረቀ ነው፡፡ ቀኝ እና ግራ ጠርዝ ላይ ቆመው በፍራቻ መተያየታቸው በመሐል ቤት የጠቀመው ሕወሓት መራሹን ቡድን ነው፡፡ የሁለቱንም ወደመሐል መምጣት መፍትሔ የሚያደርገውም አንዱ የዚህ ችግር መኖር ነው፡፡ ነገር ግን የተጣመመው እያልኩ የምጠቅሰው የኦሮሞ ብሔርተኝነት አራማጅ ልሒቃን የፈጠሩት የፖለቲካ ትርክት ከአማራ-ሰግነትም አልፎ ወደ አማራ-ጠልነት እያመዘነ ነው፡፡ የኦሮሞን ብሔራዊ ማንነትን ለመገንባት አስተዋፅፆ አድርጓል ያልኩት ‹የጋራ የመበደል ታሪክ ወለድ ሥነ ልቦና› በልሒቃኑ የተሳለበት መንገድ ‹ከታሪክ እንደምንረዳው ከአማራዎች ጋር መተማመን አንችልም፡፡ ስለዚህ አብረን አንኖርም› ዓይነት መደምደሚያ አዝሎ ነው፡፡ ድምዳሜው በአሜሪካ የባሪያ አሳዳሪ ወይም በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ ስርዓት የተበደሉ ጥቁሮች ከደረሱበትም የከፋ ድምዳሜ ነው፡፡ በጣም አሳሳቢው ጉዳይ ደግሞ በኦሮሞ ሕዝብ የዕኩልነት፣ የፍትሕ እና ርትዕ ተጋድሎ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ብዙ ቅጠል እያፈራ የመጣው ቅርንጫፍ ይህንኛው ጠማማ ቅርንጫፍ መሆኑ ነው፡፡

አማርኛ-ሰግነት
የአማራ ጠልነት ጦስ የአማርኛ ቋንቋንም ሰለባው አድርጎታል፡፡ ‹‹ሊንጓፍራንኳ›› (ባሕሩ ዘውዴ(ፕ/ር) እንዳለው) በመሆን የክልል መንግሥትን (ሕዝቦቹን) አንዱን ካንዱ እንዲያግባባ የፌደራል መንግሥት የሥራ ቋንቋነት ማዕረግ ቢቸረውም፣ የተጣመመው የኦሮሞ ብሔርተኝነት ቅርንጫፍ አራማጅ ልሒቃን ግን የአማርኛ ትምህርት ክፍለጊዜን እንዳይታደሙ (አቋርጠው እንዲወጡ) ተማሪዎቹን ያነሳሷቸዋል፡፡ የፌደራል ቋንቋው በኦሮሚያ ክልል ከ5ተኛ ክፍል መጀመሩ (ቀድሞ አለመጀመሩ) በፌደራል መንግስቱ ውስጥ ኦሮሚያን ‹‹ሐሳባቸውን እና አቋማቸውን መግለጽ በማይችሉ፣ ነገር ግን፣ በኮታ ብቻ የሚወከሉ፣ ግዑዝ ፖለቲከኞች ይሞሏታል ማለት ነው›› ያልኩት ላይ ተጨማሪ ችግር አከሉበት ማለት ነው፡፡ እነዚህ ልሒቃን ይህንን የሚያደርጉት ‹አማርኛን ከኦሮሚያ ክልል ውስጥ በ2020 ለማጥፋት› ካላቸው ምሥጢር መሆን ያልቻለ ምሥጢራዊ ዕቅዳቸው በመነሳት ነው፡፡ ኦሮምኛ ሁለተኛ የፌደራል መንግሥቱ የሥራ ቋንቋ እንዲሆን መሥራት ሌላ፣ አማርኛን ለማጥፋት መሥራት ሌላ፡፡ አንድ ግለሰብ (ወይም ማኅበረሰብ) ሁለት ቋንቋ ተናጋሪ ቢሆን ተጠቃሚው ራሱ መሆኑን የዘነጋ አካሄድ ነው፡፡ ክርክሩ ምን ያህል ውኃ እንደሚያነሳ ለአንባቢ በመተው የአማራ ልሒቃንን ከዚህ የተገናኘ ሙግት ላንሳ፡- ‹አማርኛ የፌደራል ቋንቋ በመሆኑ የተጎዳ ካለ ዋነኛው አማራ ነው፡፡ በሌሎች ክልሎች ያሉ ዜጎች ከአፍ መፍቻቸው ውጪ አማርኛን ሲማሩ፣ የአማራ ክልል ሰዎች ግን ተጨማሪ የአገር ውስጥ ቋንቋ አይማሩም፡፡ ይህም የአማራ ልጆችን ሌላ ክልል ተዘዋውሮ የመሥራት ዕድል አጥብቦታል› ይላሉ፡፡

ወደ መነሻችን ስንመለስ፣ አማርኛን ኢትዮጵያ ውስጥ ከሁሉም የበለጠ የበለፀገ እንዲሆን ያደረገው ‹‹ዕድል›› ነው፡፡ (በነገራችን ላይ በኢሕአዴግ ዘመንም የተናጋሪዎቹ ቁጥር በፍጥነት እያደገ ነው፡፡) ባሕሩ ዘውዴ “The Changing Fortunes of the Amharic Language” በሚለው ድርሳኑ ‹‹አማርኛ መበልፀጉን የቀጠለው ታሪካዊ ክስተቶች ቀድሞውኑ እንዲበለፅግ ስላደረጉት ነው›› ይላል፡፡ እውነት ይመስለኛል፡፡ መርጌታ ግሩም ተፈራ የተባለ ፀሐፊ (‹የደብተራ ታሪክ› ነው ካላላችሁብኝ) የአማርኛን ታሪክ ሲያነብር ‹የአክሱም መግባቢያ የነበረው ግዕዝ ነው፡፡ ደብተራዎች አሁንም ድረስ ‹‹ነገረ - ደብተራ›› የሚባል የሚስጥር መግባቢያ በየጊዜው ይፈጥራሉ፡፡ [በከተማ ‹የአራዳ› ወይም ‹የዱርዬ› /እንደሰሚው/ የሚባለው ዓይነት ቋንቋ ማለት ነው፡፡] ኋላ ዮዲት [አስቴር ይሁዲት] ባመፀች ጊዜ፣ አክሱማውያን መኳንንት ሸሽተው ሰሜን ሸዋ አንኮበር ተሸሸጉ፡፡ እዚያም ለሚስጥራዊነት ሲባል መኳንንቱ ‹‹ነገረ-ደብተራን›› ይጠቀሙ ጀመር፡፡ ሌላው ሰፋሪም የመኳንንት ቋንቋ አገኘሁ ብሎ ይናገረው ጀመር፡፡ በዚህ መንገድ የተወለደው አማርኛ ዕድል ቀንቶት ዕድገቱ ተፋጠነ› ይላል፡፡ (ወሬሳው ካሳ፣ 2005፡230 ላይ) የባሕሩ ዘውዴ ድርሳንም አማርኛ የተወለደው በዚሁ የ13ኛው ክ/ዘመን ገደማ እንደሆነ ይናገራል፡፡ በሌላ በኩል ዶናልድ ሌቨን (ዶ/ር) በሠራው አንድ ጥናቱ ‹አማርኛ የተፈጠረው የኦሮሞ ተወላጆች ግዕዝ ለመናገር ሲሞክሩ ነው› በማለት ያትታል፡፡ የመርጌታ ግሩም ተፈራን ትርክት ማመን ከቻልን ይህ እውነት ሊሆን ይችላል፡፡ ዶናልድ ሌቪን የአማርኛ ቋንቋ ቅርፅ (Synatax) የኩሽ ቋንቋዎች ባሕሪ ያለው መሆኑን ጠቅሶ ነው እንዲያ ያለው፡፡ ባሕሩ ዘውዴም ‹‹[አማርኛ] ተገንጥሎ ወጥቷል ተብሎ በጥቅሉ ከሚታመንበት ሴማዊው ግዕዝ ይልቅ ከኩሻዊው ኦሮምኛ ጋር ብዙ የሚጋራው ጠባይ አለው›› ብሎ ጽፏል፡፡

በዚህ ትርክት መሠረት የተጣመመው ብሔርተኝነት ቅርንጫፍ አራማጅ ልሒቃን የሚጠሉት አማርኛ፣ ምናልባትም የኦሮሞ ሕዝብ ራሱ የፈጠረው ወይም በፈጠረው ወቅት አስተዋፅዖ ያደረገለትን ቋንቋ ነው ማለት ነው፡፡ ከዚያም በላይ ኋላ የአማርኛ ተናጋሪ በመሆናቸው ‹‹አማራ›› የሚል የዘውግ ብሔር ስያሜ የሰጠናቸው ሰዎች የጥንት ዘራቸው ኩሻዊ እና አክሱማዊ (አክሱማውያን /አግኣዚኣዊያን/ ራሳቸው ኩሻውያን ነበሩ የሚባል ትርክት አሁን፣ አሁን እየገነነ ነው) የነበሩ ናቸው ማለት ነው፡፡ ፀቡ ዞሮ፣ ዞሮ ወደ ኋላ መለስ ባልን ቁጥር ከራስ የዘር ግንድ ጋር መሆኑ የተረጋገጠ እውነታ ቢሆንም የዚህን ያህል በቅርብ የሚታይ (Traceable) መሆኑ ግን የራሱ የሆነ የከንቱ ጥላቻ ፖለቲካን አስተዛዛቢ ማጋለጫ ነው፡፡

የአማራ እና የአማርኛ ጥላቻው በጥቅሉ አማራ ብለን በአሁኑ የብሔር ብያኔ መሠረት የምንጠራው ሕዝብ የሚጠቀምበትን ነገር በሙሉ በጋራ አለመጠቀም የጠማማው ቅርንጫፍ አራማጆች የላቲን ፊደሎች* ለኦሮምኛ የተመረጡት እንደ እውነቱ ከአማርኛ-ጠልነት በመነጨ ምክንያት ቢሆንም፣ ኋላ ላይ ለማስተባበል ከተጻፉ ጥናቶች የጥላሁን ጎምታን ጠቅሻለሁ፡፡ እዚያ ላይ ምናልባት አሳማኙ ‹‹ለኦሮሞ ሕዝብ የሥነ-ልቦና ነጻነት ወሳኝ ነው›› የሚለው ብቻ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጥረቱ የቴክኒክ ጉድለቶቹን የመቅረፍ ጉዳይ ብቻ ቢሆን ኖሮ የሼክ በክሪን የአፋን የኦሮሞ ፊደል ገበታ ለመጠቀም የተደረገ ጥቂት እንኳን ሙከራ (consideration) እናይ ነበር፡፡ (*በነገራችን ላይ መጽሐፌ ውስጥ የ‹ላቲን ፊደሎች› ምንጭ ነው ብዬ ‹‹የኩሽ ፊደል›› እያልኩ የጠራሁበት ቦታ አለ፡፡ ያንን ያክል ምንጭ ፍለጋ መሄዴ፣ ከሌሎች ሙግቶቼ አንፃር ምን ያክል አመክኖአዊ እንደሚያደርገኝ ራሴን በራሴ ያጠራጥረኛል፡፡ የፊደሉ ምንጭ የኔ ነው ለማለት ያንን ያክል ርቄ መሄዴ ካልቀረ ‹‹ጨቋኝ፣ ተጨቋኝ›› የምላቸውን ዘውጎችንም የሩቅ ምንጭ ቀድቼ ‹የአቤል እና ቃዬል› መጠፋፋት ዓይነት መሆኑን መግለጽ ነበረብኝ፡፡)

በነገራችን ላይ በጥላሁን ጎምታ ጥናት ላይ የተጠቀሰው በግዕዝ ፊደላት ሊቀረፍ አይችልም ከተባሉት ችግሮች አንዱ የሚጠብቁና የሚላሉ ፊደሎችን መለየት አለመቻሉ ነው፡፡ ሲጠብቁ እና ሲላሉ እንዲሁም ሲጎተቱ የተለየ ትርጉም የሚሰጡት የአፋን ኦሮሞ ቃላቶች ብዛት ምን ያህል እንደሆነ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ችግሩ አማርኛንም የገጠመው ችግር ነው፡፡ ቁቤን በመጠቀም ይህን ችግር ለመፍታት የተደረገው ሙከራም ራሱን የቻለ ሌላ ችግር ማስከተሉ አልቀረም፡፡ በግዕዝ ፊደላት አንድ ገጽ የሚጻፈው ጽሑፍ በቁቤ (ከአናባቢዎቹ መብዛት የተነሳ) ሁለት ገጽ ገደማ ይሆናል፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የተለያዩ ቦታዎች ላይ በግዕዝ ሆሄያት ፈንታ ‹‹dha,dhi . . .›› እያልኩ ጽፌያለሁ፡፡ ለምሳሌ ‹ይላማ dheeሬሳ› የሚለውን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይህንን ድምፅ የሚገልጽ የግዕዝ ሆሄ የሌለ መስሎኝ የተፈጠረ ስህተት ነው እንጂ፣ ምንም እንኳ ድምፁ በአማርኛ ቋንቋ ውስጥ ባይኖርም፣ በፊደል ገበታው ላይ ግን አለ፡፡ በነጋሶ ጊዳዳ (ዶ/ር) ታሪክ ‹ዳንዺ› ላይም ‹ዺ›ን ለመፃፍ ‹ዲ› ከጻፉ በኃላ በእስክርቢቶ አናቷ ላይ ጭረት አድርገውባታል፡፡ ነገር ግን ፊደሉ የኮምፒውተር የፓወር ግዕዝ የፊደል ሰሌዳ ላይ ‹shift key + d› ስንጫን ይገኛል፡፡ ፊደሉ ከ‹ጰ› ጋር ይመሳሰላል፤ ነገር ግን በ‹ደ› እና ‹ጸ› መካከል ያለውን ልዩነት ከተረዳን በሁለቱ ፊደሎች መካከል ያለውም ልዩነት ግልጽ ይሆንልናል፡፡ መጽሐፉ ላይ ያሉትን መሰል ግድፈቶች፣ ምናልባትም ቀጣዩ እትም ላይ አርመዋለሁ፡፡ . . . (የኦሮምኛ የግዕዝ ፊደላትን የመጠቀም ጉዳይ መሐል ሰፍረን ለምናቀነቅነው አንድነት ወይም ኅብረት ራሱን የቻለ /የአንድነት የጋራ መገለጫ/ ቅመምመሆን ስለሚችል ነው የምንቆጨው እንጂ ይህንን የምለው ወደኋላ እንመለስ ለማለት አይደለም፡፡ አንዳንዴ በአማርኛ ሆሄያት ኦሮምኛን መጻፍ ሲያስፈልገን፣ አንዳንድ የአማርኛ-ኦሮምኛ መዝገበ ቃላቶች ላይ ‹ፈፅሞ አይቻልም› እንደሚሉት ብዙም እንደማንቸገር ለማስታወስ ያክል ነው፡፡)

በአሁኒቷ ኢትዮጵያ ብያኔ አማራ የሚባለው ክልል ሕዝቦች ራሳቸውን በወንዛቸው (የኦሮሞ ሕዝብ በአብዛኛው ራሱን በብሔሩ ሥር ባለው ጎሳው መጥቀስ ነው የሚወደው)፣ አሊያም በኢትዮጵያዊነታቸው ለይተው መጥቀስ ይወዳሉ፡፡ ይህንን ግን ‹በኢትዮጵያዊነት ውስጥ የተደበቀ (pseudo Ethiopian) አማራነትን› ለማራመጃነት እንደሚጠቀሙበት መሣሪያ የሚመለከቱባቸው ብዙዎች ናቸው፡፡ መጽሐፌ ውስጥ የአማራ ሕዝብ ራሱን በአንድ የዘውግ ብሔር ማንነት ለምን እንደማይጠራ ጠቅሻለሁ፡፡ በተጨማሪም ቀድሞ ‹አማራ› ይባል የነበረው ‹አማራ ሳይንት› የሚባለው አካባቢ ብቻ እንደሆነና የአማርኛ ቋንቋ መስፋፋት ነገሩን ቀይሮ አማርኛ ተናጋሪው በሙሉ አማራ መባል እንደጀመረ› ብዙ ድርሳናት ይተርካሉ፡፡ እስከቅርብ ግዜ ድረስም ‹ማነው አማራ?› በሚለው ላይ መግባቢያ ላይ መድረስ አይቻልም ነበር (አሁንም ተችሎ መሆኑን እርግጠኛ አይደለሁም)፡፡ ለምሳሌ በፊታውራሪ ተ/ሐዋርያት ‹አውቶባዮግራፊ› ላይ ‹አማራ› የሚለው ቃል ‹ክርስቲያን› ለማለት (ገጽ 278፣ 292)፣ ‹መልካም ሰው› ለማለት (ገጽ 306) ላይ ተጠቅሷል፤ ‹የጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀ/ወልድ ማስታወሻ› ደግሞ ‹‹…የአማራ የሚባለው›› ይልና በቅንፍ ‹‹ጎጃም፣ ጎንደር›› ብሎ ‹‹ትግራይ››ን ይጨምራታል (ገጽ 10)፤ ጆን ስፔንሰር ትርሚንግሃም እ.ኤ.አ. በ1952 ባሳተመው ‘Islam in Ethiopia’ በሚለው መጽሐፉ ላይ ስለአገው ሕዝቦች ሲያወራ ‹‹አሁን ትግራይ፣ ቤጌምድር፣ ደምቢያ፣ ጎጃም፣ አገው-ምድር፣ ዳሞት እና አማራ የሚባሉት አካባቢዎች ላይ የሰፈሩ ሕዝቦች ነበሩ›› (ገጽ 48) በማለት ጎጃምና ጎንደርን (ቤጌምድርን) ሳይቀር ‹አማራ› እንዳልሆኑ ይጠቅሳል፡፡ ዛሬ ላይ ‹አማራ› ማለት በአሁኑ ብያኔ መሠረት የአማራ ክልል ሕዝብ ማለት ነው፡፡ ሒደቱ የብሔርተኝነት ብያኔን ተለዋዋጭነት ያስረዳናል ብዬ እገምታለሁ፡፡ ‹የጋራ ተበዳይነት ስሜት ለኦሮሞ ብሔራዊ ማንነት እንደሰጠው› በተደጋጋሚ ተናግሬያለሁ፡፡ በተመሳሳይ፣ የኦሮሞ ልሒቃን አማራ-ጠልነት አዝማሚያ አማራን (በተሠመረለት ድንበር ላይ ተመሥርቶ) ቀድሞ ከነበረበት እና ምናልባትም የዘመናዊ ሰውነት መጀመሪያ ነው ከሚባልለት የግለሰባዊነት (individualism) ስሜት ወጥቶ የብሔራዊ ስሜት እንዲያዳብር እያስገደደው ነው፡፡ ይህ የምሥራች አይደለም፡፡

ደም አዳኝነት
‹‹ኦሮሞነትን በደም የሚገልጽ ካለ ለኔ ሞኝ ነው›› ብያለሁ፡፡ ሞኝ ብቻም አይደለም፤ አደገኛም ነው፡፡ የተጣመመው የብሔርተኝነት ቅርንጫፍ አንዱ አደገኛ መገለጫ ይኸው ኦሮሞነትን በደም ለመግለጽ መሞከር ነው፡፡

ኦሮሞ ማነው?
ሀ) ኦሮሞ ማኅበረሰብ ውስጥ ከኦሮሞ ወላጆች ተወልዶ ያደገ፣ ቋንቋውን የሚችል፣ ባሕሉን የሚረዳ፤
ለ) ኦሮሞ ማኅበረሰብ ውስጥ ኦሮሞ ካልሆኑ ወላጆች ተወልዶ ያደገ፣ ቋንቋውን የሚችል፣ ባሕሉን የሚረዳ፤
ሐ) ከኦሮሞ ማኅበረሰብ ውጪ ከኦሮሞ ወላጆች ተወልዶ፣ ቋንቋውን የማይችል፣ ባሕሉን የማይረዳ፤
መ) አፋን ኦሮሞ የሚናገር፣ ባሕሉን የሚረዳ ማንኛውም ሰው፤
ሠ) ኦሮምያ ክልል ውስጥ የሚኖር ማንኛውም ሰው፤
ረ) . . .

በጣም አደገኛ የሚባለው መልስ ማንነትን በደም ለመግለጽ መሞከር ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሙከራ ንፁህ ዘር፣ ድቅል ዘር... ወደሚል መደምደሚያ ያመራል፡፡ ቀድሞ በነበረው ጅምላ ፍረጃ (stereotyping) ላይ ተመስርቶ፣ በክፉ ቀን፣ ውጤቱ ዘር ማጥራት ነው፡፡ Genocide! ማንነትን በደም ለመግለጽ መሞከር ማንነት በአንድ በኩል የቋንቋ፣ የባሕል እና የሙያ ውህድ ውጤት፣ በሌላም በኩል በትምህርት፣ በጉብኝትና ልምምድ የሚለዋወጥ (ተፈጥሯዊ ያልሆነ ሥሪት) መሆኑን ሰርዞ ‹በዘር ሐረግ የሚመዘዝ ነገር ነው› እንደማለት ነው፡፡ ‹ሰውዬው፣ ለምሳሌ ኦሮሞነትን በደሙ፣ ከወላጆቹ ካልወረሰ አፍ መፍቻ ቋንቋውም ሆነ የሚያውቀው ባሕል የኦሮሞ ብቻ የሆነ ሌላ ቋንቋ የማያውቅ ሰው ኦሮሞ አይደለም ሊባል ነው› እንደማለት ነው፡፡ በርካታ የኦሮሞ ብሔርተኝነት አራማጅ ድረ-ገፆች ላይ የሚታየው ግን ይህ ነው፡፡ አንድ የኦሮምያ ክልል ባለሥልጣን በተሾመ ቁጥር ድረ-ገፆቹ የሰውዬውን ወላጆች ማንነት ጎልጉለው በማውጣት ‹‹ኦሮሞ አይደለም›› ብለው ይጮሃሉ፡፡ ሰውዬው ‹‹ኦሮሞ ነኝ›› ካለ፣ ‹ኦሮሞ ነው› ያለው የኦነጉ በያን አሶባ (ፒ.ኤች.ዲ) አባባል፣ አባባል ብቻ ሆነ ማለት ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥም እንደተገለጸው ሙክታር ‹‹የም›› ነው ይባላል፡፡ እሱ ‹‹ኦሮሞ ነኝ›› ማለቱ የጠማማው ቅርንጫፍ አራማጆች እንዲቀበሉለት አላደረጋቸውም፡፡ መረራ ጉዲና የአምቦ ሰዎች ‹‹ኦህዴድ አልጋችን ላይ የተወለደ ዲቃላ ነው›› አሉኝ ሲል፣ ‹በደም ኦሮሞ አይደሉም› በሚል ኦሮሞነት እየተነፈጉ ነው ማለቱ መሆን አለበት፡፡ ይህ በራሱ በጉዲፈቻ እና ሞጋሳ፣ የደም ውርስ ሳያስፈልግ ኦሮሞነትን ለሚያጎናጽፈው ጥንታዊ ባሕል ዲቃላ አስተሳሰብ ነው፡፡ የደም ቆጠራ አደገኛ አዝማሚያ የሚንፀባረቀው ራሱን የኦሮሞ ብሔርተኝነትን በሚጎዳ መልኩ ጭምር ነው፡፡ ለምሳሌ የሙክታር ከድር እና የአስቴር ማሞ አመራር ‹‹የጅማ መንግሥት›› መባሉ፣ ቀድሞ ደግሞ ኤርሚያስ ለገሰ እንደነገረን ‹‹አርሰናሎች›› (የአርሲ ሰዎች) አመራር በዛ መባሉ የዘር ቆጠራው፣ ብሎም የሥልጣን ክፍፍሉ ወደ ወንዝ ቆጠራ እንደሚወርድ አመላካች መርዶ ነው፡፡ (እንደጉዳይ የተነሳው የሥልጣን ክፍፍሉ አለመማከል ሳይሆን የሰዎቹ የትውልድ ቀዬ ጉዳይ በመሆኑ!) ዞሮ፣ ዞሮ የዘር ቆጠራው ዓላማ የቡድን መብትን ማስከበር ሳይሆን ‹‹ብሔርተኞች›› የሚፈልጉት አካል ሥልጣን እስኪቆጣጠር የሚመዙት ካርድ ሆኖ እንደሚቀጥልም ማመላከቻ ይሆናል፡፡

ዘውገኝነትን ወይም ብሔርተኝነትን (ጥቂት ነው ልዩነታቸው) ምሁራን በሁለት ሊከፍሉት ይሞክራሉ፣ በመልካምነቱ እና በክፋቱ፤ ዘውጌኝነት /ዘውጌ እኝኝነት/ (ethnocentrism) እና ዘውጌኛነት /ዘውጌ እኛነት/ (Nationalism) - ሁለቱም ትርጉሞች ለዚሁ ጽሑፍ ሲባል፣ መጽሐፉ ላይ የበፍቃዱ ሞረዳ ‹ማነው ዘረኛ?› ግጥም በመዋስ ፈጥሬ የተጠቀምኩባቸው ናቸው፡፡ ዘውጌኝነት ‹እኔ የምወከልበት ዘውግ ከሌሎች ዘውጎች ሁሉ ምርጡ ነው› በማለት ከሌሎች ጋር በዘር ላለመቀየጥ መሞከር፣ ሌሎችን ማግለል እና መጠየፍ እንደመፍትሔ የሚወስዱትን የሚወክል ሲሆን፤ ዘውጌኛነት ግን ለዚህ ጽሑፍ ሲባል ‹እኔም ሆንን ሌሎች ዕኩል የሰው ዘሮች ነን፤ ሆኖም እኔ ይወክለኛል የምለውን ዘውግ መምሰል ነው የምፈልገው› በሚል የዘውጉን ቋንቋ፣ ባሕላዊ አለባበስ እና አኗኗር ዘዬ የሚያዘወትሩትን የሚወክል ነው፡፡ በዘመነ ሉላዊነት (globalization) ግን ይህ የሚቻል ዓይሆንም፤ ሰዎች እንደኩሬ ውኃ በአንድ ቦታ ረግተው በሚኖሩበት ዘመን፣ ከሌሎች ጋር አለመቀየጥ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነበር፡፡ ለሰዎች ዓለማቸው አካባቢያቸው ነበር፡፡ አሁን ግን ሰዎች፣ ግለሰዎች እየሆኑ ነው፡፡ ይንቀሳቀሳሉ፤ ይቀየጣሉ፤ ባሕል፣ ቋንቋ፣ ወግና ሥልጣኔ ይወራረሳሉ፤ ያሻቸውን ካላሻቸው ይመርጣሉ፡፡ እንደየዘመኑ አንዱ ባሕል፣ ቋንቋ ወይም ሥልጣኔ ከሌላው የበለጠ የገነነ እና ተቀባይነት ያለው ይሆናል፡፡ የዘመኑ ሰዎችም (ትውልዶችም) የበለጠ የገነነውን እና ተቀባይነት ያለውን በመምረጥ የበለጠ ተጠቃሚ ሆነው ያልፋሉ፡፡ 

መጽሐፉ ውስጥ የሆነ ቦታ የገለጽኩላችሁ የባስክ ፖለቲከኞች አባዜ (የተጣመመው ቅርንጫፍ) ብሔርተኞችም አባዜ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ የአፍሪካ ኅብረት (ወይም የምሥራቅ አፍሪካ አካባቢያዊ ትብብር) መጠናከርን እየፈለጉ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር ግን አብረን አንኖርም የሚል እርስበርስ የሚጋጭ አስተሳሰብ ነው፡፡ የአፍሪካ ኅብረት 50ኛ ዓመትን አስመልክቶ የታተመው ‹‹Unite or Perish›› የሚል የጥናቶች መድብል ላይ ‹‹Separatist Movements, Insurgencies, and Integeration in Africa›› በሚል ርዕስ በHanji A. Diyal የተሠራ ጥናት እንዲህ ይላል፡-
‹‹በመላው አፍሪካ ልሒቃን የመንግሥት ሥልጣን ለመቆጣጠር በማለም በግጭቶች ተጠምደዋል፡፡ የመንግሥትን ሥልጣን የመያዝ ግልጽ ዓላማው የገዛ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ማሻሻል ነው፡፡ በአፍሪካ የመንግሥት ሥልጣን ለልሒቃኑ እውነተኛ የሀብት ማፍሪያ እና ማስጠበቂያ ሰርተፍኬት ሆኗል፡፡ በርግጥ፣ የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ማለት የዘውግን ጥቅም ማስተማመን ከሚለው ጋር ትርጉሙ አንድ ሆኗል፡፡›› (የኔ ትርጉም፣ ገጽ 322)
መራር እውነት ነው፡፡ ስለዚህ በስመ ብሔርተኝነት (ወይም ዘውገኛነት) የሚቀነቀኑ ‹‹የደም›› ማጣራቶች አላማ ለግል ጥቅም የመንግሥትን ሥልጣን መሆኑ መጋለጥ ይኖርበታል፡፡ ብሔርተኝነት ፍትሕ እና ርትዕን ለማረጋገጥ እንጂ በማኅበረሰቦች መካከል ሐሳባዊ መለያ መሥመር ለማኖር መዋል የለበትም፡፡

በተለይ ከቅርብ ግዜ ወዲህ በግልፍተኝነት እና በግልብነት በተደረሱ ድምዳሜዎች ተነሳስቶ አንዱ ዘውገኛ፣ ሌላውን ሲገፋ - ዛሬ፣ ዛሬ መሠረታዊ የሰው ልጅነት በአገራችን ዋጋ አጥቶ በብሔርተኝነት እና ተጠቃሚነቱ የጎደለ የሚሉት ዘውግን ጥቅም በማስከበር ሥም የራስን ጥቅም ማሳደድ የተለመደ ሆኗል፡፡ ልብበሉ! ችግሩ የኦሮሞ ልሒቃን ብቻ አይደለም፤ በተለይ ከበፊቱ በከፋ አሁን፣ አሁን እያቆጠቆጡ ያሉት የአማራ ብሔርተኛ ልሒቃንም (አቀራረቡ ቢለይ እንጂ)፣ የሌሎችም ጭምር ነው፡፡ ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛ የሚባሉትም ሳይቀሩ የዘውግ ብሔርተኞቹን እሴት የኢትዮጵያውያን አድርጎ የመቀበል የተሳሳተ ዕይታ እየተጋረጠባቸው ማየት የተለመደ ነው፡፡ የተጣመመው የብሔርተኝነት ቅርንጫፍ ወረርሽኝ እያጠቃ ያለው ሁሉንም ነው፡፡ …በአገራችን ሁሉም ጎጡን ሲያሳድድ እንደፖለቲካው ሁሉ ተራው የሸቀጥ ግብይት በዘውገኝነት እንዲመራ እያደረገ ያለው የተጣመመ ብሔርተኝነት ነው፡፡ በአገራችን የሰውዬውን ስም ሰምቶ ብቻ የፖለቲካ አመለካከቱን ብቻ ሳይሆን ገንዘብ የሚያስቀምጥበትን ባንክ፣ የሚጠጣውን የቢራ ዓይነት፣ የሚደግፈውን የአገር ውስጥ የእግር ኳስ ቡድን ሳይቀር መገመት እየተቻለ ነው፡፡

ለራሳችን ከእንግሊዝ፣ ስፔን፣ ላቲን አሜሪካ ድረስ የሚካሄዱ የእግርኳስ ሊጎችን እየተከታተልን፤ የቻይናና ሕንድ ጅንሶችን እየለበስን፤ የሆሊውድ፣ ቦሊውድ እና ኖሊውድ ፊልሞችን እየኮመኮምን፤ ከሶቅራጠስ እስከ ዘርዐያቆብ እያጣቀስን እንኳን የዘውግ ብሔርተኝነት፣ ዘውጎቹን ያቀፋቸው ኢትዮጵያዊነትም ይጠበናል፡፡ ዓለማዊ፣ ሰብኣዊ ነን፡፡ የተጣመመ ብሔርተኝነት ያመጣብን አባዜ፣ መፍትሔው ወደኋላ በመጓዝ ከታሪክ አይቀዳም፡፡ ጥላቻም ተረኛ ጨቋኝ ይፈጥር እንደሆን እንጂ መልስ አይሆነንም፡፡ ዶ/ር ሌቪን ‹ትልቋ ኢትዮጵያ› በሚለው መጽሐፉ ‹‹በልዩ ልዩ ቀለማት አሸብርቃ እንደተጠለፈች የጥልፍ ሥራ ሁሉ ኢትዮጵያም ፈፅሞ የተለያዩ ሕዝቦች ጥልፍ ትመስላለች ብሎ ማሰብ ሕዝቦቿ ለዘመናት እርስ በርሳቸው የነበሯቸውን በርካታ ግንኙነቶች፣ በጋርዮሽ የተካፈሉትን መከራና ደስታ መዘንጋት ነው›› ይላል፡፡ ...ኢትዮጵያ ለተበደሉት ሕዝቦቿም፣ ለጨቋኝ ልሒቃኖቿም ከተራ ጥልፍ በላይ የማይተረተር የብሔረሰቦች የርስበርስ ትስስር ነች ነው ነገሩ፡፡ ሼክ በክሪ ሳጳሎ ደግሞ ‹‹የወደፊቷ ኢትዮጵያ ሕልውና የሚወሰነው በኦሮሞ ሕዝብና በሌሎች ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዕኩልነት እና አንድነት ነው›› ብለው ነበር፡፡ ልብ በሉ! ‹‹በሕዝቦቹ እኩልነት እና ዕድገት ነው›› ያሉት፡፡ ሁለት በአንድ! ይህ እውን የሚሆነው ጠማማው ቅርንጫፍ ዛፉን ከማጉበጡ በፊት እንዲቃና ማድረግ (righting the wrong) ከቻልን ነው፡፡
---
ማስገንዘቢያ: በጽሑፉ የተጠቀሱት ምሁራን አንቱ ያልተባሉት ጽሑፉ ‹የኦሮሞ ጉዳይ› ለተሰኘው መጽሐፍ ምላሽ እንደመሆኑ የመጽሐፉ ደራሲ በተጠቀመት መንገድ ለመጻፍ ሲባል ነው፡ የዚህ ጽሑፍ ዋና ቅጅ በጥቅምት 20/2008 በኢትዮ ምኅዳር ጋዜጣ ላይ የታተመ ነው፡፡