Showing posts with label መዝናኛ. Show all posts
Showing posts with label መዝናኛ. Show all posts

Tuesday, September 10, 2013

የ2005 የጊዜ መሥመር


በማሕሌት ፋንታሁን

ክቡራት የዞን 9 ነዋሪዎች ዓመቱ ከማለቁ በፊት እንዴት እንዳለፈ ለማስታወስ እንዲረዳን በማሰብ በ2005 የተከናወኑ አበይት ተግባራትን በዓመቱ የጊዜ መሥመር ላይ እንደሚከተለው ለማሳየት ሞክረናል፡፡ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ፡፡

መስከረም
  • §  መስከረም 11/2005 የተከበሩ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ሆነው፣ የተከበሩ ደመቀ መኮንን ደግሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሐላ ፈፀሙ፣
  • §  መስከረም 17 ቀን 2005 ድምፃዊ ቴድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በሒልተን ሆቴል አንድ ሺሕ ያህል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ጋብቻውን ፈፀመ፣

ጥቅምት
  • §  ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ አሜሪካን ሃገር ከሚገኘው የዓለም አቀፉ የሴቶች ሚዲያ ፋውንዴሽን የ2012 ‹ፅናት በጋዜጠኝነት ሥራ› የተሰኘ ሽልማት አገኘች፣
  • §  የ2005 የእስልምና ምክር ቤት /መጅሊስ/ ምርጫ በየቀበሌው ተካሄደ፣  

Wednesday, October 3, 2012

የሴቶች ወጪ <=> የወንዶች ገቢ



ሴቶች በዝግመተ ለውጥ ካለመቆጠር ወደ መቆጠር ከመቆጠርም አልፈን ‹ከስኬታማ ወንድ ጀርባ አንዲት ጠንካራ ሴት አለች› የሚባልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡ ተፈጥሮና ባህላችን ተደማምረው አሳማኝ ምክንያት ሳይኖር የሴትና የወንድ የሆኑ ነገሮች እንዲለዩ ሆነዋል፡፡ የሥራ ዘርፍ፣ የትምህርት ዘርፍ፣ አለባበስ፣ አነጋገር፣ አካሄድ፣ አጻጻፍ፣ ባሕሪ፣ አመለካከት… ሁሉም የሴት እና የወንድ የሚባሉ አሏቸው፡፡ ጥልቅ የመመራመር ክህሎትን በሚጠይቁ ዘርፎች ተሰማርተው የሚገኙ አንዳንድ ሴቶች የተቀረነውን ወክለው የተቀመጡ እንጂ እንደወንዶቹ እራሳቸውን ብቻ ወክለው አይደለም፡፡ ለምሳሌ ‹የመጀመሪያው የወንድ ጄኔራል› የሚባል ነገር ሰምተን አናውቅም፡፡ ‹በመጀመሪያ ወደጠፈር የተጓዘው ወንድ› ሲባል ልንሰማም አንችልም፡፡ ምክንያቱም መጀመሪያውኑ ወደ ጠፈር የመጓዝ ተግባር እና የጦር አዛዥነት ሥራ የወንድ ብቻ ተደርጎ ስለሚቆጠር እና በዘርፉም የሴቶች ተሳትፎ ከወንዶቹ ጋር ሊነፃፀር የሚችል ስላልሆነ ነው፡፡

በአገራችን ከተለመዱና የወንዱ ተግባር ተደርገው ከሚቆጠሩ ነገሮች አንዱ ወጪዎችን የመሸፈን ኃላፊነት ነው፡፡ እስካሁን ድረስ ‹ሴትማ አትከፍልም› እየተባለ የከፋይነት ሥራ የወንድ እንደሆነ ቀጥሏል፡፡ ማኅበረሰባችን ለወንድ የወጪ ሸፋኝነት ኃላፊነት ሲሰጥ በውስጥ ታዋቂነት ጥሮ ግሮ በሚያፈራው ኃብት የሚመሰርተውን ቤተሰብ የማስተዳደር ሥራ ከሱ እንደሚጠበቅ ይረዳዋል፡፡ ስለዚህም በተሰማራበት ዘርፍ ጠንክሮ በመሥራት ገቢውን ማሻሻል የሕይወት ዘመኑ መመሪያው ይሆናል፡፡ ከሴት የሚጠበቀው ጥሩ ሚስት እና እናት እንድትሆን ነው፡፡ የራሷ ገቢ የምታገኝበት መተዳደሪያ ወይም ሥራ ያላት ብትሆንም እሰየው ነው፤ ባይኖራትም ግን ችግር የለውም፡፡ እንዲኖራት አትገደድም፡፡

ወንድየው ወደፊት ለሚያገባት ሚስቱና በጋራ ለሚያፈሯቸው ልጆች ማስተዳደር እንዲችል ገቢውን ለማሳደግ እና ኃብት ለማፍራት ተግቶ ይሠራል፡፡ ‹ቤት ሳይኖረኝ› ‹ቋሚ ሥራ ሳልይዝ› ‹ጥሩ ደሞዝ ሳይኖረኝ› የሚሉ ወንዶች እንጂ ሴቶች እምብዛም አይደሉም፡፡ ባጭሩ ማኅበረሰባችን ለሴቶችና ለወንዶች ብሎ ሁለት የተለያየ የተግባር መንገድ አስቀምጦልናል፡፡ በሴቷ መንገድ የሚገኙ ወንዶች  እንዲሁም በወንዱ መንገድ የሚገኙ ሴቶች ቢኖሩም በአብዛኛው ሴቱም ወንዱም በተመደበለት መንገድ ነው የሚንቀሳቀሰው፡፡ ይህ አመዳደብ ወንዶችን የሴቶች የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስቴር ሆነው በበላይነት እንዲመሩን ያደርጋቸዋል፡፡ እኛ ሴቶችም በአብላጫ ድምፅ ያፀደቅንላቸው ይመስላል፡፡

Thursday, August 9, 2012

ሎሚ ሽታ… መጽሐፍ አንደ ፊልም

ሶሊያ ሽመልስ
መጀመሪያ ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ስነሳ ሙሉ ለሙሉ የፊልም ተመልካች አስተያየት ብቻ እንሆነ ይቆጠርልኝ፡፡ ባለሞያነት ሲያልፍም አይነካካኝ! ባይሆን የጥበብ አፍቃሪ ዕይታ ነገር ነው በሉና ውሰዱልኝ፡፡

የአማርኛ ፊልሞች ላይ ተስፋ ከቆረጥኩ ከራርሜለሁ፡፡ ታዲያ አንድ ከሃገር ገባ ወጣ የሚል ጥበብን በምንም ሁኔታ የሚያደንቅ ወዳጄ (እየተበሳጨም ቢሆን) እግሩ ወጥቶ በገባ ቁጥር የአገርኛ ፊልሞችን አብሬው እንዳይ ይጋብዘኛል፡፡ የእርሱን ጨዋታ ፍለጋም የፊልሞቻችንን ለውጥ ለማየትም ያህል በርሱ ግብዣ ክፍተት ልክ ነው አማርኛ ፊልሞችን የማየው፡፡ ታዲያ እነርሱም አይቀየሩም፣ እኔም አልቀየርም፤ እበሳጫለሁ፣ ያበሳጩኛል፤ ጓደኛዬን ተነጫንጬበት ቆይታችን ያበቃል፡፡ ተመሳሳይ ሁነቶችን በተመሳሳይ ስሜቶች እያስተናገድን እንደጋግማለን፡፡ እርሱ ፊልሙ ጥሩ ጎን ባይኖረው እንኳን ፈልጎ (ምንም ጥሩ ጎን የሌለው ፊልም የሚሰራባቸው አገራት መካከል መቼም ዋነኞቹ ነን፡፡ ይህንንም እንግዲህ እንደለመድነው፤ ከዓለም አንደኛ ምናምን ብለን ገጽታ ለምን አንገነባበትም?)  ይሔንን እንደዛ ቢያደርጉት እኮ ጥሩ ፊልም ይሆን ነበር፣ ትንሽ አክቲንጉን እያለ… ማጽናኛ ቢጤ ሊነግረኝ ይሞክራል፡፡ በዚህ የአገርኛ ፊልሞች ብስጭቴ ነበር ከወራት በፊት የአዳም ረታ እቴሜቴ ልቦለድ ወደ ፊልም እየተቀየረ እንደሆነ የሰማሁት፡፡ እውነቱን ልናገርና ከፋኝ! አዳም ምን ነክቶት ነው ለፊልም አሳልፎ የሚሰጠን ያውም እቴሜቴን ብዬ ለጥቂቶች ነግሬያለሁ፡፡ ኧረ እንደውም በፊስቡክ ላይ ራሱ ስጋቴን አስቀምጬ ነበር!

(ስለ አዳም ሌላ ቀን እናወራ ይሆናል ስለ እቴሜቴ ግን ዝም ብዬ አላልፍም፡፡ ከኢ-ፓለቲካዊ ንባብ ከራቅኩ ቆይቻለሁ፡፡ እንደውም ትቼዋለሁ ማለት ይቀላል፡፡ አዳም ረታ ሲሆን ግን ሁሉም ነገር ሌላ ይሆናል፡፡ በጽሑፉ፣ በፊልሙ፣ በመጽሐፉ፣ በቲያትሩ በሁሉም ቦታ የሚታየውን አገራዊ ዝቅጠት ለማረሳሳት የቀረልኝ ብቸኛ ማጽናኛ ነው፡፡ እቴሜቴ ደሞ የብዙዎቻችን (በተለይ የሴቶቹ) ታሪክ በዘመን፣ በዓይነት እና በሰፈር ተከፋፍሎ የተቀመጠበት ምርጥ ሥራው ነው፡፡ ሆ…… ስለእኔ ነው እንዴ የሚያወራው አስብሎኛል፡፡ ያውም ብዙ ጊዜ! ይህንን የምንጊዜም ምርጥ መጽሐፍ ነው አዳም ለሐበሻ ፊልም ሠሪ የሰጠብኝ ብዬ ነበር የተከፋሁት!)