Friday, September 26, 2014

የአምስት ወራት የግል ማስታወሻ

ያ ትውልድ ያመነበትን ተግባራዊ ለማድረግ ብዙ መስዋዕትነትን እንደከፈለው ሁሉ እህት በወንድም ላይ ጠቁማ ወደ ሞት የነዳችበትም አጋጣሚዎች ተፈጥረዋል ወንድም ከወንድም ጋር የሚያፋጅ ግዜ ላይም ነበሩ፤ ዛሬ ላይ እንደቀልድ ምንሰማው ለመፍረድም ቀላል የሚመስሉትአስቀያሚ የታሪኮቻችን አጋጣሚዎች ዛሬም ላይ ይከሰታሉ እኛም ስህተቶችን የምንደግም እንጂ ከስህተቶቻችን የምንማር ዓይነቶች አይደለንም፡፡
ከኢህአዴግ ወገን ላልሆነው ፖለቲካ የሚወደድ ሆኖባይሆንም በአገር ጉዳይ ያገባኛል ያሉ ሰዎች የሚገናኙባቸው ቦታዎች የተለመዱ ናቸው እስር ቤት፣ ሰላማዊ ሰልፍ(እጥረት ቢኖርብንም)እንዲሁም ፌስቡክ የመጀመሪያውን ተርታ ይይዛሉ፡፡ እንደውም ማህበረሰብ ሚዲያው እርስ በርስ ለመግባባት ለመገማገምና  ለመተዋወቅ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡ በኤዶም ካሳዬ እና በእኔ መካከልም ትውውቅምክንያት የሆነውና በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኘነው ወደ ቂሊንጦ እስር ቤት ለመሄድ ከተሰባሰቡት የዞን ዘጠኝ አባላት ጋር ተሰባስበን በነበረበት ወቅት ነበር ወዲያውም ኤዲ ጆማ ተባብለን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ሞቅ ወዳለው የፖለቲካ ጨዋታ ስንገባ አይተውን የተጠራጠሩት ጓደኞቻችን ከዛሬ በፊትም ሳትገናኙ አልቀራችሁም አይነት ትንኮሳ ጀምረው ነበር የምንታጨቅበት ታክሲ ሲመጣ ወሬያችን ቢቋረጥም፡፡
Journalist Edom Kassaye
ከቂሊንጦው እስር ቤት የጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ጥየቃ በኋላ በተለያዩ አጋጣሚዎች ተገናኝተን ተጨዋውተናል፣ እንደውም በአንድ ወቅት በጨዋታችን ውስጥ ደጋፊና ተቃዋሚ ጥግ እና ጥግ (አንዳንዴም ጽንፍ) የያዙ ፍረጃዎች ኑሮ ፈተና ለሆነባቸው የቤተሰብ ሃላፊዎች ስራቸው አስተማማኝ ይሆን ዘንድ አባልነት ግዴታ ሆኖባቸው አባል የሆኑትንና ያልሆኑት ግን ውሳኔዎችን ለማስቀየር ምንም ዓይነት አቅም እና ስልጣን የሌላቸው ነገር ግን በተቃውሞ ጎራ በካድሬነት የመፈረጅና የመዘለፍ አጋጣሚዎችን ያስተናገዱ ሰዎች ስለመኖራቸውና አንዳንዶች በብሔር ፖለቲካ ቅርቃር ውስጥ ተቸንክረው ወደ መከላከልና ጽንፍ የያዙ ደጋፊ ሆነው ስለመገኘታቸው እንዲሁም በኑሮ ውድነት ምክንያት መቃወም እየፈለገ ቤተሰቡን ማስተዳደር ፈተና ሆኖበት ከቤት ኪራይና ከሌሎች ወጪዎች የሚናጡ ባልና ሚስቶች ብሶትን መሰረት አድርገን መሃከል ላይ ስለምንገናኝበት አልያም የእነኚህን ሰዎች ስሜት ሌሎች እንዲረዱ ለማድረግ አንድ ጽሁፍ በጋራ ለመጻፍ ሁሉ ተመካክረን ነበር፡፡

በጋዜጠኛነት በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶችውስጥ ያሳለፈችው ኤዶም ከዞን ዘጠኞችና ከእነ አስማማውና ተስፋለም ጋር ስትከሰስ የግድ ዞን ዘጠኝ ነሽ እያሉ ነበር በሕግ የሚቀልዱትፖሊሶች የከሰሷት፡፡

ከዛ በፊት ግን ዞን ዘጠኝ ባትሆኚም ከእነሱ ጋርስለምትቀራረቢ መረጃ ስጪን እያሉ የገባችበት የሚገቡ በስልክ ፋታ የሚያሳጧት “ደህንነቶች” ነበሩ፤ ኤዲ በአንድ ወቅት የሆነ መስሪያ ቤት ስራ ለማመልከት ጎራ ብላ ስትወጣ አፍታም ሳይቆይ ይደወልላታል በዚህ ወቅት የደወለው ደህንነቱ ነበር የመስሪያ ቤቱን ባለቤትስም ጠርቶ “ ሥራ እንዳመለከትሽ ሰምቼያለሁ ከእኛ ጋር እኮ ብትተባበሪ የተሻለ ደረጃ በተሻለ ደሞዝ አስቀጥርሻለሁ” ብሏት ነበር፤በተደጋጋሚ ወቅትም “ዞን ዘጠኞች ለምን መጻፍ አቆሙ የተደበቀ ህቡህ ሥራ ስለጀመሩ ነውና መረጃ እንድትሰጪኝ እፈልጋለሁ አለበለዚያ ውጪ አገር ስብሰባ ላይ መንግስትን ለማሳጣት የተናገርሻቸውን ምክንያት አድርገን ልናስርሽ እንችላለን አንቺ ብቻ ተባበሪን እንጂ ወደ ውጪም መሄድ ከፈለግሽ አሜሪካም ሆነ አውሮፓ ምንም ችግር የለውም ትሄጃለሽ አንቺ ብቻ ተባበሪን “ የሚሉ ማስፈራሪያዎችና ማግባቢያዎች ይቀርቡላት ነበር ፡፡ ኤዶም በመልሷ “እኔ እስከማውቀው ልጆቹ ምንም እየሰሩ አይደለም ትልልቅ ሆቴል ውስጥ ኢንተርኔት ነጻ ስለሆነ እና ሰውም ስለማይበዛ ማኪያቶ  እየጠጡ የሚጨዋወቱናቸው መጻፍ ስላቆሙ ጓደኝታቸው ተቋረጠ ማለት ስላልሆነ ይገናኛሉ ከመንግስት ጫና ስላበዛችሁባቸው እንዲሁም በግል ምክንያቶቻቸውእንጂ ሌላ ነገር ስላሰቡ አይደለም” ብላ መልሳላቸው ነበር፡፡ የደህንነቶች ክትትል አሁንም የተባበሪና መረጃ አምጪ ትዕዛዝ ለረጅም ጊዜ ፋታ አልሰጣትም ነበር ፡፡በአንድ ወቅት ስብሰባ ላይ ሆና ስልክ ባለማንሳቷ የገባችበት እንደሚገባ እና እንደማታመልጣቸው ከዛቻ ጋር የጽሁፍ መልዕክት ተልኮላት እነደነበር ትዝ ይለኛል፡፡
ደህንነቱና አለቆቹ የሆነ ነገር እየተካሄደ ነው የሚል ስጋት መስከራቸው ምንም የሚያጠያይቅ አልነበረም፡፡ ( እኛም እነደ ቡድን አውነቱን ሲያውቁ ይተውታል የሚል የዋህነት ነበረብን) እናም ኤዶም የምታቀርበው እውነተኛ መረጃ ከሌለ በፈጠራም ቢሆን እንድትተባበራቸው ግፊት ሲደርጉባት የቆየ ቢሆንምለእንደዚህ አይነት ርካሽ ተግባር ተባባሪ ባለመሆኗ የጅምላ እስሩ ተቋዳሽ ሆናለች፡፡ የእኔም መትረፍ ያለኤዶም እና ናትናኤል ፈለቀ(ናቲ) የሚቻል አልነበረም፡፡ “freedom of expression ትሰራላችሁ ወንጀል አንደሆነ አታውቁም?” የሚሉ የእውቀት ደረጃቸው ለመግባባት አንኳን የሚያስቸግሩ ሰዎቸን እነ ኤዲ ለወራት ለማሳመን ሲጥሩ ከርመዋል፡፡
በታሰሩ ቀን ማግስት በነበረው ቅዳሜ ጠዋት ላይ በቅርቡ የልጅ አባት የሆኑትን ወዳጆቼንለመጠየቅ ከሰአት በኋላ ከዞን ዘጠኞች ጋር ቴስት ኦፍ አዲስ የምግብ ፌስቲቫልን ለመታደም ማታ ላይ የቴዲ አፍሮን ኮንሰርት ለመታደምአስቀድሜ አቅጄ የነበረ ቢሆንም ሰው ያስባል ኢህአዴግ ያስራል ሆነና የሕይወቴ አንዱ እና ትልቁ የምለው ብዙ ወንድሞቼንና እህቶቼን በእስር ያጣሁበት ማግስት ሆነ፡፡
#TimeStandStill pic edited by Mahilet Solomon
ጊዜው አምስት ወራት ተቆጥረዋል ቢልም ለብዙዎቻችን እንደቆመ ነው፣ ንጹህ ኅሊና ያላቸው ለትውልድ ምሳሌ የሚሆኑ ጓደኞቼን ህገ መንግስታዊ መብት ባልተከበረበት፣ የህግ የበላይነት እና የህግ ስርአት መመራት ቀልድ በሆነበት በስርአቱ አገልጋዩች መነካታቸው ያንገበግበኛል፣  ለኔ ጊዜው አሁንም እንደቆመ ነው ሻንጣዬ ውስጥ ያለውን እቃ አውጥቼ ቁምሳጥን ውስጥ ለመጨመር አዲስ ሕይወት ከጀመርኩ እነሱን የምረሳ እየመሰለኝ እንዳለ አለ ተመልሶ እነሱን እንደሚያገኝ ለጉዞ እነደተሰናዳ ሰው ልቤ እንደተሰቀለ እስካሁን አለሁ፡፡ ይህ እኔም ሆነ የተረፍነው ወዳጆቼ የምንጋራው ስሜት ነው፡፡
ራሳቸውንም ሆነ ቤተሰባቸውን የሚያኮራ መከራን ለመጋፈጥ የቆረጡ እውነተኛና ሃቀኛ ሰዎች ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል፤ እነሱንም የወለዱ እናትና አባቶች ሊኮሩ እንጂ ሊያዝኑ አይገባም፡፡

ኤዲ ያንቺ ጓደኛ ስለሆንኩ ኩራት ይሰማኛል፡፡
 #TimeStandStill #FreeZone9Bloggres #FreeEdom#FreeTesfalem #FreeAsmamaw #FreeAllPoliticalPrisoners

Saturday, September 20, 2014

Confessions of the Ex-‘Revo’

Befekadu Hailu


There was a time in my life when I used to think a lot about revolution in Ethiopia. In fact, in 2011 during the so called ‘Arab Spring’ I wrote a rejoinder article when Ethiopian democracy activists (especially those who are based in diaspora) planned a ‘Day of Rage’ using Facebook and aimed at ending EPRDF’s two-decade authoritarian rule. Just after a year I wrote one more rejoinder titled “Revolution is Ephemeral ’. In this article I tried to highlight what Ethiopians truly lack to launch a genuine social revolution using social media. In these couple of articles it appeared that I went up against proponents of revolution but I was trying to explain the traceable causes and conditions of social revolution. In a nutshell, I was saying that the significant portion of the Ethiopian population, the opposition politicians, and the intellectuals and generally the elite and social ideals and social reality were not sufficiently prepared to kick-start an authentic and organic social change.
Yet again in 2012, I was inspired enough to write a series of articles under a general title ‘Concerning Change’ on our own blog Zone9. In the first of my series of articles titled “Will EPRDF hand over power by means of election?”  I tried to explain why EPRDF will keep on clinging to power. I argued that EPRDF is not yet ready for an electoral democracy. In a bid to demonstrate an alternative yet constitutional means of possible social change such as civil disobedience I wrote further articles as a follow up to my critique and highlighted different elements of social change across a spectrum of societal issues. As much as I can  I tried to kindle genuine public conversations in bringing these issues to the public’s attention through my articles such as ‘Fear and Social Change’ ‘Regime Change and Religion’, ‘The Role of Civil Society in 1974 Ethiopian Revolution’ and “Revolution or Sluggish Change”  It was during this time that I contemplated deeply about revolution. It was one phase of my life in which I have tried to articulate my comprehension of revolution into pieces of writings but it was also a stage of my life in which my belief on revolution was dropped off significantly.  But I have to confess here that my belief on revolution plummeted to its all-time low merely in 2013. Subsequently, I found myself turned into an activist of an organic social change through processes (not a transient revolution) from an avid reader and advocate of revolutionary ideas.  I have to put in plain words that what made me skeptic of transient revolutions; I have to explain at length that how I progressed (say it regress if you like) from being optimistic revolutionary to a proponent of an organic and authentic social change through processes, as the 1960s Ethiopian Marxist revolutionaries put it, what turned me from being ‘Revo’ (revolutionary) to ‘Sabo’ (Saboteur). Please note that I was only an enthusiastic reader of revolutionary ideas.  
  At some stage while I was grappling with the revolutionary ideals of intending to bring fundamental structural change in favor of the mass but unexpectedly might turn to be like unrestrained wildfire which could be destructive; Mohamed Morsi was ousted in Egypt's second revolution just in two years. The second Egyptian rebellion (revolution) made me feel perplexed about revolutions. But I thought in his short-lived presidency Morsi operated against basic principles of democracy and hence I believed the second revolution was born in resistance to another form of dictatorship. Certainly the second revolution even made me assert “A Conscious public will not be a possession of a despot and Egyptians are a proof”. I genuinely took the idea seriously that Egyptians would thrive in protesting until they get their preferred form of government; just like the 18th century series of French Revolutions which profoundly affected modern history. However, I realized that this is not the case when I observe the Egyptian army suspended the constitution and took control the revolution. In a similar manner of the 1974 Ethiopian Revolution during which the Ethiopian army  hacked the revolution the Egyptian army did the same. After that I even went as far as asking “If Revolutions are inherently similar?” 
In the meantime the Ethiopian social media sphere and the private press spontaneously embarked on entertaining a sort of peculiar conversations. These conversations were prompted by Jawar Mohamed’s public comment on Al Jazeera’s English daily television program called The Stream. On the show when Jawar was pressed by the host of the show what he prefers, flanked by his ethnic and national identity; he declared his ethnicity comes first over his national identity and acknowledged himself as ‘Oromo First’. Many consider the public discussion which followed the Jawar incident as a pointless exercise of talking past each other but I think of this spectacle in a different way.  I consider this incident as one of fascinating things because it really helped many people to re-examine their understanding of Ethiopia’s historical and political phenomenon. For me that incident was an excellent opportunity and serves as an evidence that we need a ground for long-running debates and a continuous scholarship on Ethiopia’s historical and political phenomenon. The spectacle should be an eye opening and insightful opportunity especially for those of us who are a loosely-knit community of dissents, oppositions groups, writers and activists whose organizing purpose is only to triumph over EPRDF. It was an incident that tasked all of us to find a possible way and build a system that can maintain a consensus among opponents. Furthermore, the incident made it clearer than ever that most of us only know what we do not want but we do not clearly know what we really want. To conclude on this, the incident exposed that Ethiopians struggle for democracy is not principled but rather it is based on indignation and grudge.  
As difficult as this issue to contemplate I started to realize the fact that despotic leaders are generally results of broader and yet fundamental societal flaws. For me this was like the aha! moment. So when revolution is conceived in a society with a high degree of authoritarianism, the end result is usually more authoritarianism. I think it comes down to individual elite who appeared liberal and revolutionary from authoritarian society are either concealed  authoritarian themselves or the society is not yet ready to allow  them to exercise their liberty. This is like a classic causality dilemma, which one came first a chicken or the egg.  But I think one should change first and it should be the society. It is with this eureka effect that I tried to revisit the revolutions in the Arab world. Tunisia, Egypt, Libya, and Syria… and I tend to think that the revolutions in these countries have done more harm than good. They caused a great deal of human suffering. Removing a despot does not necessarily guarantee a change. In similar manner the 1974 Ethiopian Revolution which removed HaileSelassie’s rule and replaced with the Dergue, a Marxist military junta is just as bad (If not worse) than the revolutions of the Arab world. It is even worse if we consider the human suffering that was caused by the infighting and power struggle of the political parties of the time. I have watched when the storied Ukraine for its Orange revolution of 2004 back to revolution all over again in 2014. I even tweeted about it ‘to revolution then calmness and back’. The February 2014 Ukrainian revolution culminated (I am not sure if I can say it is culminated) in turning over its own State Crimea to pro-Russian forces even though it appeared the Russian involvement in Ukrainian affairs cited as one of the cause of the revolution. I also wrote a commentary on my personal blog asking Are revolutions meant to be betrayed? ››My point in this particular blog post was showing reasons why elite citizens who usually initiate revolutions would end up in brawl and infighting after they started revolutions. I used the old Amharic saying to illustrate my point ‘Thieves usually do not fight when they steal but they brawl when they divide what they robbed”.  I intentionally used the word ‘thieves’ to illustrate the context of Ethiopian political reality. I am referring to Ethiopian astroturf political originations (formal or informal) that are organized in the name of interest group to bring social change. Beyond their being astroturf in their nature they fight each other. We have numerous such groups and their sole propose is to get hold of political power and harvest the benefits from it not brining genuine revolution.

For this reason I truly believe we can bring change without going through an instantaneous revolution. We can take a good lesson from the history of English people. The English people have a lot of exemplary deeds. Rule of law, discussion and public engagement though grass root organizations can bring the desired form of government and we can also achieve social change peacefully.
An acquaintance of mine who knows my stance of instantaneous social change came to visit me in prison after I was unjustly accused of inciting revolution.  He looked at me and said " Aha, what did I told you, there will never be a change without revolution’. But remarkably even in the injustices and sufferings me and my zone9 blogging collective colleagues have been through I still see the need for an authentic social change. Had the society have had the consciousness; they would have seen the impunity of the Ethiopian government (police) enjoy and the injustice we are suffering from. Apparently the Ethiopian government does not have the slightest concern for legitimate questions of Ethiopians but rather they are deeply bothered by the ‘noise of foreign powers’.   Suffering the consequence of using the right to freedom of expression has become a social reality because the society sits silently and watches all the injustice. Society should start to speak up against injustice but to do so we should embark on educative and liberating process through grassroots activism and peaceful disobedience which are yet not happened in Ethiopia. Once a society has become conscious of the benefits of liberating social change and developed a test for liberty there is no way back. I believe consciousness comes first then liberty follows. We have failed spectacularly because as a society we have the cart before the horse in most of our projects.  That is how explained for my acquaintance who visited me in prison as well. However, as Kiflu Tadesse put it on the first of two volumed books “That Generation” which dealt with the 1974 Ethiopian Revolution Haile Fida one of the iconic figures of the storied Ethiopian Socialist Movement never predicted Ethiopians would revolted just one year ahead of the 1974 Ethiopian Revolution. According to Kiflu, in 1973 Haile said for Ethiopians to start a revolution it would take them a minimum of twenty five years. Unless I blunder like Haile I don’t think there will be a revolution in Ethiopia in the foreseeable future. Finally like the Ethiopian satirist Abebe Tola usually say if I screw-up on this screw me over. 

Thursday, September 18, 2014

የቀድሞው “የአብዮት አድናቂ” ኑዛዜ (“Confession of the Ex-Revo” )

በፍቃዱ ዘ ኃይሉ
 
ርዕሱን  አላስታውሰውም ‘ንጂ እ.ኤ.አ በ2011 Arab Uprising በመባል የሚታወሰውን አብዮትተከትሎ፣ ኢትዮጵያውያን ፌስቡከኞችም (በተለይ ዲያስፖራ የሚገኙ) ግንቦት 20 ላይ (ልክ በኢሕአዴግ የ20ኛ አገዛዝ ዕድሜ)   “Anger day” በሚል በፌስቡክ አብዮትመጥራታቸውን ተቃውሜ አንዲት ጽሑፍ ጽፌ ነበር፡፡ በዓመቱ ደግሞ ‹‹ አብዮት ወረት ነው›› በሚል ርዕስ በፌስቡክ አብዮት ለማስነሳት ፍላጎት ያላቸው በርካቶች እንዳሉ ገልጬ ነገር ግን ይጎድላቸዋል የሚባሉትንነገሮች ዘርዝሬ ጽፌ ነበር፡፡ በነዚህ ሁለት ጽሑፎች ላይ፣ ላዩን አብዮትን የተቃወምኩ ቢመስልም እውነታው ግን ጽሑፎቹ በተጻፉበትወቅት ሕዝቡም፣ ተቃዋሚ ልሂቃኑም፣ ሁኔታዎቹም ለአብዮት ዝግጁ አይደሉም የሚል ዝንባሌ ማሳየቱ ነበር፡፡
ከሌላ ዓመት በኋላደግሞ ‹‹ስለለውጥ›› በሚል ርዕስ ተከታታይ ጽሑፎችን በ‹‹ዞን 9›› ላይ በግል ተነሳሽነት ማስፈር ጀምሬ ነበር፡፡ ጽሑፉን የጀመርኩት ‹‹ኢሕአዴግ ሥልጣኑን በምርጫ ይለቃል?›› በሚል ጥያቄ ነበር፡፡ ‹‹አይለቅም›› የምልባቸውን ምክንያቶች ካስቀመጥኩ በኋላ የለውጥ አማራጭ የምላቸውን (አብዮት፣ሰላማዊ አለመታዘዝ /civil disobedience/ የመሳሰሉትን) በየዘርፉ እየቀነጫጨብኩ ለማሳየት ነበር ዓላማዬ ከዚያም ‹‹የለውጥ ፍርሃት››፣ ‹‹የሥርዓት ለውጥ እና ሃይማኖት››፣ ‹‹የ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት እና የማኅበራት ሚና›› የሚሉ ርዕሶችን በማንሳት በሐሳቦቹ ላይ በሐቀኝነት ለመከራከር ጥረት አድርጌያለሁ (ከዚህ በላይ አልገፋሁበትም እንጂ)፡፡ በበኩሌ ስለአብዮት በደንብ ያነበብኩትም፣ ያሰብኩትም፣ የጻፍኩትም፣ የተረዳሁትም ያኔ ነበር፡፡ ያኔ በአብዮት ላይ የነበረኝ እምነት ተሸርሽሮ ግማሽ ደርሶ ነበር፡፡ ተንጠፍጥፎ ያለቀው ግን አሁንም በዓመቱ (በ2006 አጋማሽ) ነው፡፡ አንባቢ ከአብዮት አድናቂነት ወደ ዝግመተ ለውጥ አራማጅነት (በ ‹‹ያ ትውልድ›› ሰዎች አጠራር ከRevo ወደ Sabo) የተሸጋገርኩበትን የሐሳብ ዳገት (ከፈለጋችሁ ቁልቁለት በሉት) ይረዳ ዘንድ በመጠኑ ዘርዘርአድርጌ ማስረዳት አለብኝ፡፡ (ታዲያ አብዮት አድናቆቱም ቢሆን ከወረቀት እንዳላለፈ ልብ በሉልኝ)፡፡
እነዚያን ተከታታይ ጽሑፎች በጻፍኩበት ሰሞን  ‹አብዮት ‹‹እቆጣጠረዋለሁ›› ብለው ያሰቡትንነገር ግን ድንገት ከቁጥጥር ውጭ ሊሆን የሚችል እሳትን መለኮስ› እንደሆነ እያሰብኩ ባለሁበት ሰሞን ግብጻውያን ሙርሲን ለመጣል ያምጹ ጀመር፡፡ የግብጹ ድጋሚ አመጽ (አብዮት) በጣም የተዘበራረቀ ስሜት ፈጥሮብኝ ነበር፡፡ ሙርሲ እኔ በግሌ ከማምንባቸውና ቋሚም ከሆኑ የዲሞክራሲ መርሆች እያፈነገጠ ነበር፡፡ ስለዚህ የግብጾች ማበይ ምክንያታዊ ነው ብዬ አምኛለሁ፤ እንዲያውም ሕዝብ አንዴ ‹ከነቃ አይሆንም ዕቃ› ብዬ ነበር፡፡ የግብጽ ሕዝብ የሚፈልገውን ዓይነት ሥርዓት እስከሚያገኝ እያበየ ይቀጥላል የሚል ግምት ነበረኝ- ልክ እንደ ፈረንሳዮቹ ተከታታይ አብዮቶች፡፡  ነገር ግን የግብጽ ሕዝብ እያበየ ቢቀጥልም እንኳን የፈለገውን ላያገኝ እንደሚችል የተረዳሁት ወታደራዊ ክንፍ ቀስ በቀስ አገሪቱን በአብዮቱ ተከልሎ ሲጠቀልላት ስመለከት ነበር ፡፡ ከአገራችን የደርግ አመጣጥ አልለይ ብሎኝ ‹አብዮቶች ሁሉ አንድ ናቸው እንዴ?› እስከሚያስብል ድረስ ተመሳስሎብኝም ነበር፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ሚዲያ እና ፕሬሶች በአንዳች ተዋስኦ ይናጡ ጀመር፡፡ ተዋስኦው የተጀመረው የጃዋር መሐመድን ‹ኦሮሞ ቅድሚያ›(Oromo First) የአልጄዚራ ምላሹን ተከትሎ ነበር፡፡ ብዙዎች ይሄን ወቅት የሚያስታውሱት እንደአላስፈላጊ የንትርክ ወቅት ቢሆንም፣በበኩሌ ብዙዎች ቆም ብለው አቋማቸውን እና የአቋማቸውን መሠረት እንዲፈትሹ፣ በታሪካዊ እና ፖለቲካዊ ኩነቶች ላይ ንባባቸውን እንዲቀጥሉ ያስታወሰ መልካም አጋጣሚ ነው ባይ ነኝ፡፡ ይህ አጋጣሚ በስመ ተቃዋሚ (dissent) የአንድ ኢሕአዴግን ከሥልጣን መውረድ ብቻ እንደ ለውጥ ግብ አድርገን በጋራ ስንንቀሳቀስ የነበርን ተቃዋሚ ግለሰቦች እና ቡድኖች እርስ በርስ ያሉትን ልዩነቶች እና ልዩነቶቻችንን የምናቻችልባቸውን መንገዶች እንድናስተውል መንገድ ፈጥሯል፡፡ ብዙዎቻችን የማንፈልገውን እንጂ የምንፈልገው ምን እንደሆነ በቅጡ እንደማናውቅ፣ትግላችን ከመርሕ ይልቅ በእልሕ እንደሚመራ ያጋለጠ፣ ራሳችንን እንድንገመግም ያስገደደ አጋጣሚ ነበር፡፡
ከዚህ ድንጋጤ ውስጥነው ‹አምባገነን መሪዎቻችን ከሕዝብ ጉያ የወጡ› የአስተሳሰብ ችግር የወለዳቸው የመሆናቸው ሐቅ ዘልቆ የገባኝ (ወይም genuinely comprehend ማድረግ የተቻለኝ) ስለዚህ አብዮት ሲፀነስ ዓላማው ባልተለወጠ ሕዝብ ላይ የተለወጠ መሪ ማስቀመጥ ቢሆንም ሲወለድ ግን አንድም ያልተለወጠ ሕዝብ የተለወጠ መሪ መውለድ ስለማይችል፣ አንድም ደግሞ የተለወጠ መሪ እና ያልተለወጠ ሕዝብ  መዋሐድ ስለማይችሉ፣ አብዮቱ (ዓላማው) ይጨናገፋል፡፡
በዚሁ ጊዜ ነበር የቅርብጊዜ ምሳሌያችንን የአረብ አብዮትን መልሼ በወፍ በረር ለመገምገም የተገደድኩት፡፡ ቱኒዚያ፣ ግብጽ፣ ሊቢያ፣ ሶሪያ…. ከተሳካው የከሸፈው፣ከለማው የወደመው ይበዛል፡፡ የአምባገነን መገርሰስ ብቻውን ለውጥ አያመጣም፤ ከነዚህኞቹ ለውጦች ይልቅ የእኛው ፊውዳሊዝምን ገርስሶ- ወታደራዊ አምባገነንነትን ያመጣው አብዮት የተሻለ ኪሳራ ነበረው ማለት ይቻላል፡፡ (እዚህጋ በኢሕአፓ፣ መኢሶን እና ሌሎችም የደርግ ፓርቲዎች መካከል የተደረገው የድኅረ አብዮት የሥልጣን ሽኩቻ ሳቢያ የጠፋውን ሕይወት ሳንቆጥር መሆኑ ነው፡፡) ከትንሽ ጊዜ በኋላ ደግሞ በብርቱካናማ አብዮቷ የምትደነቀው ዩክሬን አበየች፡፡(‹“የተውኩትን ነገር ተነግሬ፣ ተመክሬ ባገር ምን ጎትቶ አመጣብኝ፣ የአብዮትን ነገር?" Another revolution? ብዬ ትዊት አድርጌም› ነበር) አብዮቷ ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ የአካሏ ክፋይ የሆነችው ክሬሚያን በማሳጣት ይጀምራል፡፡ ምዕራብ ዩክሬናውያን ሲያብዩ ‹የአገራችን መንግሥት ከምዕብራባውያን ይልቅ ምስራቃውያን (ራሺያ….) አደላ› ብለው ቢሆንም በውጤቱ ግን ጭራሽ ራሺያ ክሬሚያን ጠቅልላ አረፈችው፡፡ልብ በሉ! አብዮቱ ከተነሳበት 360 ዲግሪ ዞሮ ተጠናቀቀ፡፡ ለነገሩ አልተጠናቀቀም፤ አሁን ወደ እርስ በእርስ ጦርነት ተሸጋግሯል፡፡
ይኼኔ ነበር በግል ጦማሬ ላይ ጥር 2006 ‹‹Are revolutions meant to be betrayed?›› ብዬ በመጠየቅ የጻፍኩት፡፡ ዜጎች አብዮትን ሲጀምሩት የማይታዩ ችግሮች ሲጨርሱት የሚስተዋለው ‹ሌባ ሲካፈል እንጂ ሲሰርቅ አይጣላም› ነበር የጽሑፌ አንኳር ሐሳብ፡፡ ‹‹ሌባ›› ያልኳቸው  በሕዝባዊ አብዮት ስም የግል ሕልማቸውን የሚያሳኩ አጀንዳ ያላቸውን ቡድኖች (interest groups) ነው፡፡ በኢትዮጵያ ነባራዊ የፖለቲካ እውነታ ደግሞ እነዚህ ዓይነቶቹ interest groups ብዙ ናቸው፡፡ ስለዚህ በአብዮት ለውጥ አማጭነት ተስፋ ስቆርጥ የመጀመሪያ ጥያቄዬ ‹‹ሳያብዩ ለውጥ ማምጣት ይቻላል?›› የሚል ነበር፡፡ የመጀመሪያ መልሴ ‹‹እንግሊዝ›› ነበረች፡፡ የእንግሊዝ ሕዝብና መንግሥት በሕግ የበላይነት ላይ ለማንም ምሳሌ መሆን የሚችል ነው፡፡ የዓለምን ግማሽ በገዙበት ጊዜም አሁንም አብየው አያውቁም- እንግሊዛውያን፡፡ ምክንያቱም ተወያይተው ችግራቸውን መፍታት ይችላሉ፡፡ ሕዝብና መንግሥት ሲለወጡ ሁሉም በሰላም ይካሄዳል፡፡
ይህንን የመጨረሻ አቋሜን ያውቅ የነበረ ወዳጄ፣ ‹‹እህ አሁንስ?›› አለኝ ‹አብዮት ልታስነሳ አሲረሃል› ተብዬ ተጠርጥሬ ከታሰርኩ በኋላ  ሊጎበኘኝ መጥቶ፡፡ ‹‹አየኸው አይደል፣ ያለአብዮት ለውጥ እንደማይመጣ?›› የሚገርመው፣ የኔና የጓደኞቼ በሕገ-ወጣዊ ማንአለብኝነት መታሰርና፣ የመንግሥት (ፖሊስ) ተጠያቂነት ማጣት ውስጥም ሕዝባዊ አለመለወጥ ነው የሚታየኝ፡፡ መንግሥት አሁንም ቢሆን የሚያስጨንቀው ‹‹የውጭ ኃይሎች ጫጫታ›› እንጂ የውስጥ ሰዎች ጥያቄ አይደለም፡፡ በእኛ ላይ የደረሰው (ሐሳብን በመግለጽ ጦስ መታሰር) በሌሎች ላይ ሲደርስ የነበረ፣ እየደረሰ ያለ ፣ ወደፊትም የሚደርስ መሆኑ ቢታወቀውም ሕዝባችን ግን ‹‹መብቴን ማስጠበቅ አለብኝ›› ከማለት ይልቅ ‹‹ዝም ብል ይሻለኛል›› (ጎመን በጤና) mode ውስጥ ነው፡፡ ሕዝብ ገና አልተለወጠም፤ የለውጥ ጣዕሙም የገባው አይመስልም፡፡ ሌሎች ሰላማዊ የትግል አማራጮችም ገና በኢትዮጵያ አልተሞከሩም፡፡ ሕዝቡ ጣዕሙን የማያውቀውን ለውጥ ከመስጠት በፊት ደግሞ የለውጡን ጣዕም አውቆ ለውጡን ራሱ ጠይቆ፣ ራሱ እንዲያመጣው ማንቃት ያስፈልጋል፡፡ አለበለዚያ እንግሊዛውያኑ እንደሚሉት ‹ጋሪው ከፈረሱ ቀድሞ› አይሆንም! ለወዳጄም ይህንኑ ሃሳቤን ነበር የነገርኩት፡፡
ለነገሩ ይህንን ሁሉአልኩ እንጂ ክፍሉ ታደሰ በ‹‹ያ ትውልድ›› (ቅጽ 1) ላይ  ‹ኃይሌፊዳ በ1965 በኢትዮጵያ በ25 ዓመት ጊዜ ውስጥ አብዮት ይነሳል ብዬ አልገምትም ብሎ ነበር› እንዳለው ካልሆንኩ በቀር እኔም በቅርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ አብዮት ይነሳል የሚል ምንም ግምት የለኝም፤ በመጨረሻም በአቤ ቶክቻው ዋዘኛ አባባል ‹‹ካጠፋሁ፣ልጥፋ!››

Tuesday, September 9, 2014

የዞን9 ጦማር "የስጋት" መስመር

ይህ አመት አንደተለመደው አይነት አመት ቢሆን ኖሮ በዚህ ወቅት የዞን9 ጦማርያን በጦማሪት ማህሌት አስተባባሪነት ፣ በአጥናፍ ብርሃኔ እና በጆማኔክስ ካሳዬ ትብብር የአመቱን ታላላቅ ክስተቶች አሰባስበው ከመታተሙ በፊት ለቡድኑ ክለሳ የሚያቀርቡበትና የተረሱ እና ለክስተትነት የማይበቁ የምንላቸውን ሁነቶች የምንለይበትና የአመቱን የጊዜ መስመር የምናወጣበት ወቅት ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን ያንን ከማድረግ ይልቅ የዞን9 የጦማርያን ቡድን የጊዜ መስመርን በመስራት ያለፈው አንድ አመት አሁን በስደት እና በእስር የሚገኙት ወዳጆች አንዴት አሳለፉት የሚለውን ለመግለጽ ወደድን፡፡  ይህ የጊዜ መስመር የመጨረሻው የዞን9 ኢትዮጲያዊ ህልም ዘመቻ ከተካሄደ በሁዋላ ባለው የ2006 ዓ/ም በዞን9 ዙሪያ የነበሩ ነገር ግን ለአደባባይ ያልበቁ ክስተቶቸን ይዘግባል፡፡ አላማውም አመቱ አንደቀልድ አለማለፉን እና በአደባባይ ያልተባሉት ጉዳዪች ምን እነደነበሩ ለዞን9 ነዋሪያን ግንዛቤ ያህል ከብዙ በጥቂቱ የቀረበ ነው ፡፡

መስከረም 2006 –አራት የዞን9 ጦማርያን የተሳተፉበት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በኢትዮጲያ ምን ይመስላል የሚል ሪፓርት ዝግጅት ተጠናቀቀ፡፡ በሪፓርቱም ላይ ሃሳብን የነጸነት የመግለጽ መብት ምን ይመስላል የሚለውን ሪፓርት ለተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሚያዝያ ኢትዪጵያ መንግሰት ላይ ለሚያደርገው ዩንቨርሳል ፔሪዲክ ሪቪው (UPR)- የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሰባአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ የሀገራት የእርስ በርስ መገማገሚያ ስነ ስርአት  የሚቀርብ  (ለሚዲያ የማይቀርብ ለተባበሩት መንግሰትት ብቻ የሚገባ) ሪፓርት ነበር፡፡
በሪፓርቱ ከተሰራ በሁዋላ ጦማርያን ጓደኞቻቸውን እና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ላይ ጠንካራ አቋም አላቸው የሚሏቸውን የገዢውን ፓርቲ ደጋፌዎች በመጨመር የሪፓርቱን ውጤት አሳይተው ግብረ መልስ ተቀበሉ፡፡ በወሩ መጨረሻም ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስረከቡ፡፡ (በዚህ ሂደት በሁዋላ ለደህንነት አካላት የወዳጆቸን እንቅስቃሴ በመንገር አየር መንገድ ላይ ሲወጡ አንዲጠየቁ ያደረገው የሪፓርተሩ ጋዜጠኛ የማነ ናግሽ የዚህ ሪፓርት ዝግጅትም ንቁ ተሳታፌ ነበር፡፡ )

 በዚሁ ወር የዞን9 ጦማርያን ወዳጅ የሆኑ የተለያዩ አጋር አካላት መንግሰት ጦማርያኑን ከግንቦት ሰባት ጋር በማያያዝ ስማቸውን እያነሳ ነው በሚል ለጦማርያኑ ጉዳዩን ግልጽ አንዲያደርጉላቸው ጠየቁ፡፡ በማስከተልም   የዞን9 ጦማሪ እንዳልካቸው ሃይለሚካኤልን ለትምህርት ከአገር መሄድ አስመልክቶ በተደረገ የምሳ ግብዣ ላይ የቡድን የደህንነት ጉዳይ የውይይት ርእስ ሆኖ ተነሳ ፡፡ በወቅቱ ብዙ የዞን9 ጦማርያን መንግስት አንደ አደጋ አይቆጥረንም የሰራነውም ወንጀል የለም፣ ያለን እንቅስቃሴም ኢንተርኔት ላይ የተገደበ በመሆኑ የደህንነት( እስርም ሆነ የስደት ) ስጋት የለብንም በሚል ተከራከሩ፡፡ በተቃራኒው ቢሆንም አንዲህ አይነት የመንግስት አረዳድ ላይ ችግር ካለ ለጊዜው ለሚቀጥሉት ወራት አንቅስቃሴያችንን በማቀዝቀዝ የመንግሰት ጥርጣሬ አግባብ አለመሆኑን ለማሳየት እንሞክር የሚል ሌላ ክርክር በመምጣቱ ሃሳቡ ተቀባይነት አግኝቶ ውሳኔ ላይ ተደረሰ፡፡ በመሆኑም የበይነ መረብ ዘመቻዎች ለተወሰነ ጊዜ አንዲቆሙ ፣ ወደአፍሪካ ኮሚሽንም ሆነ ወደተባበሩት መንግስታት አንዲሁም የኢንተርኔት አራማጅነትን አስመልክቶ ልምድ ለማካፈል የሚደረጉ ማንኛውም አይነት አለም አቀፍ ጉዞዎች ( በጣም አስፈላጊ እና ቀድመው የታቀዱ ካልሆኑ በስተቀር) አንዲተላለፉ ተወሰነ
በዚሁ ወር አጋማሽ ጦማሪ እነዳልካቸውለፒኤች ዲ ትምህርት ወደአሜሪካን አገር ኦሪጎን ዪንቨርሲቲ አቀና፡፡

በዚሁ ወር መጨረሻ ሁለት የዞን9 ወዳጆች እና አጋሮች ከአዲስ አበባ ኤርፓርት ለመውጣት ሲሞክሩ ኢሜግሬሽን ላይ ካገር አንዳይወጡ ለተወሰነ ሰአት ተይዘው የተለያዩ ጥያቄዎች ቀረበላቸው ፡፡ ሁለቱም ወዳጆች ላይ በተደረገው ድንገተኛ ምርመራ ከዞን9 ጦማርያን ጋር ያላቸውን ግንኙነት አንዲያስረዱ ተጠየቁ ፡፡

ጥቅምት/ ህዳር 2006 - ጦማርያኑ በዞን9 በኩል የሚጻፉ ጽሁፎችን አቀዝቅዘው በግል የማህበረሰብ ሚዲያው ላይ ወጣ ገባ ሲሉ ቆዩ፡። በዝምታው ቆይታ በጦማርያኑ የታየ ይህ ነው የሚባል የአደባባይ ስራ ቢኖር አሜሪካን አገር ለሚገኘው የኤንፒአር ኮጆ ሾው ኢትዮጲያ ውስጥ በትችት ድምጽ መጦመር ምን ይመስላል የሚለውና የሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በኢትዮጵያ የሚለው አርቲክል 19 በተባለው መንግስታዊ ያልሆነ የሰብአዊ መብት ድርጅት የተሰራው ዶክመንተሪ ፊልም ላይ ተሳትፎ ማድረግ ብቻ ነበር፡፡


ታህሳስ 2006  - በዚህ ወር በተደረገ ስብሰባ የታየ በቂ ደህንነት ችግር ስለሌለ ስጋታችን የተጋነነ ነውና ወደተለመደው አንቅስቀሴያችን መመለስ አለብን የሚል ውይይት ተካሄደ፡፡ ወደ ሥራ ለመመለስ የጋራ እቅድ ለማውጣት እና የተለመዱ የዞን9 ስራዎችን ይዞ መመለስ ይገባል የሚል ሃሳብ ተነስቶ ለመመለስ የሚያስፈልጉ ዘመቻዎች እቅዶች እና አዳዲስ ጉዳዮቸን የማስተዋወቅ እቅድ አንዲወጣ የስራ ክፍፍል ተደረገ፡፡  ተያይዞም ኢንተርኔት ላይ የዞን9 ህጋዊ ምዝገባን ለማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ ባለመኖሩ በተለያየ መልክ በመመዝገብ ይበልጥ ወደ ማህበረሰባዊ ስራ መጠጋትና ተቋማዊ ማድረግ ይገባል ተብሎ ተወሰነ፡፡ በ6 ወር ጊዜ ገደብ ውስጥም ወደሚዲያ/ሲቪል ሶሳይቲ ለማሳደግ ያሉትን እድሎች የማየት እቅድም አብሮ ተያዘ፡፡  በተመሳሳይ ወር አቶ አቤል አባተ አቀናባሪነት በመንግሰት ደህንነትና በኢትዮጲያ ቴሌቪዥን ድጋፍ የዞን9 ጦማርያን ላይ የተነጣጠረ የቀለም አብዩት የተሰኘው አሳፋሪ ሃሳብን የሚያቀርበው የቴሌቪዥን ዶክምንተሪ ታየ፡፡ (በወቅቱ በጦማርያኑ መካከል በተደረገ ውይይት ከዶክንተሪው በፌት ዞን9ን ይመለከታል የሚል ግምት መጀመሪያም አሳድሮ ነበር፡፡ )  

ጥር 2006 - ጦማሪ ናትናኤል ከአንድ ራሱን ከብሄራዊ ደህንነት አንደመጣ ባስተዋወቀ ሰው በመኖርያ ወረዳው አስተዳደር አማካኝነት ጥያቄ ቀረበለት፡፡ በወቅቱ ጥያቄው ስለጦማሪ ናትናኤል የፓለቲካ ተሳትፎ ስለዞን9 ምስረታ፣ አላማ ፣ እና አባላት የመሳሰሉት ሲሆኑ የደህንነት አባሉ የዞን9 አባላት 10፣000 ናቸው አላማችሁ ምንድነው? የአገር ደህንነትን የሚነካ ነገር እየሰራችሁ እንዳልሆነ በምን እናውቃለን የመሳሰሉ ጥያቄዎችን ያካተተ ነበር፡፡ ናትናኤል የዞን9 አላማ እና የሚሰራቸውን ስራዎች በዝርዝር አስረድቶ አባላቱ 9 አንደሆኑ 10.000 የተባሉት የዞን9 የፌስ ቡክ ገጽ ላይክ ያደረጉት ናቸው በማለት አብራራለት፡፡ የደህንነት አባሉ የቡድን አደረጃጀት ምን ይመስላል? ድጋፍ ታገኛላችሁ ወይ የመሳሰሉትን ጥያቄዎች በመጠየቅ ናትናኤልን አብረኸን እንድትሰራ አንፈልጋለን የሚል ጥያቄ አቀረበለት፡፡ ናትናኤል በወቅቱ ከደህንነት ጋር የሚያሰራ ምንም ችሎታ አንደሌለው ሌላ ጊዜ ቢጠየቅም ተመሳሳይ መልስ አንደሚመልስለት[JK4]  በማሳወቁ ደህንነቱ ወደፌት እናወራለን በማለት ተለየው፡፡ በዚህም የተነሳ በዚሁ ወር የታቀደው ጽሁፎችን እና ዘመቻዎችን ይዞ የመመለስ ውሳኔ ጉዳይ በድጋሚ ላልተወሰነ ጊዜ ተራዘመ፡፡ በተመሳሳይ ወር ከታሳሪዎች አንዳቸው ከናትናኤል ጋር ተመሳሳይ የሆነ የደህንነት ጥየቃ አስተናገዱ ፡፡ በወቅቱ ከአሁን ታሳሪዎችን አንዱን ያናገረው ሌላ የደህንነት አባል  የሚሰሩትን ነገር ሪፓርት አድርጉልን እየተከታተላችሁ በመናገር አብራችሁን ስሩ የሚል ጥያቄ አቅርቦ ነበር፡፡

የካቲት 2006 - በዚሁ ወር መጨረሻ ጦማሪት ሶልያና ሽመልስ ሰብአዊ መብት አማካሪ ፌሎ በመሆን በቀጣዩ የኢትዮጲያ ሰብአዊ መብት ግምገማ ጋር ተያያዥ የሆኑ ስራዎቸን ለመስራት ለመስራት ተጓዘች፡፡ በጦማሪያኑ በተደጋጋሚ የሚገናኙባቸው ቦታዎች ላይ በግልጽ እና በሚታይ መልኩ የደህንነት ሰዎች አዘውትረው መታየት ጀመሩ፡፡ በተመሳሳይ  ወር ጦማሪ ሶልያና ቀድማ የምትሰራበት መስሪያ ቤቶች ሃላፌዎች ጋር የደህነት ሰዎች የተለያዩ ጥያቄዎችን አቀረቡ፡፡ በዚሁ ወር በተመሳሳይ ናትናኤል እና በሌላ አሁን ታሳሪ ላይ ላይ የሚደርሰው ወከባ (በአካልም በስልክም) በረታ ከሚጠየቁት ጥያቄዎችም መካከል አላማችሁ ምንድነው ? ከነማን ጋር ነው የምትሰሩት? በፓርላማ ከታገዱ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላችሁ ወይ ? ባለፉት ወራት ዝም ያላችሁት ለምንድነው ? እየሰራችሁ ያላችሁት ሌላ ስራ አለ ወይ? የሚሉ ነበሩ፡፡ በወቅቱ የተነሱት ጥያቄዎች አላማችሁ ምንድነው? አባላታችሁ አደጃጀት አላችሁ ወይ የሚሉ ተደጋጋሚ እና አሰልቺ ሲሆኑ ጥያቄ ፣ የደህንነት አባላቶቹ ስለ ኢንተርኔትም ሆነ ስለማህበረሰብ ሚዲያ ያላቸው እውቀት በጣም አነስተኛ በመሆኑ ግማሹ ጊዜ መሰረታዊ የማህበረሰብ ሚዲያን አሰራር በማስረዳት የሚያልቅ ሲሆን በአንድ ወቅት አንዱ የደህንነት አባል ፍሪደም ኦፍ ኤክስፐረሽን ትሰራላችሁ የሚል ክስ በማቅረቡ በተመጣጣኝ ደረጃ መነጋገር አስቸጋሪ እየሆነ ነበር፡፡


መጋቢት 2006-  ከአሁን ታሳሪዎች አንዱ ላይ  አሁን ዝም ያሉት ለምንድነው?  የሚሰሩት ሌላ ነገር ስላለ ነው የሚሉ ጥያቄዎቸን በተደጋጋሚ አስተናገዱ፡፡ ፣ በዚሁ ወር ነገሮች መክፋታቸውን ተከትሎ ለዞን9 ጦማርን ለሌሎች ልምድ እንዲያካፍሉ በተጋበዙበት በታንዛንያ በተደረገው ስብሰባ ውጪ ያሉ የዞን9 ጦማርያን በስካይፕ የተሳተፉበት ሰፋ ያለ ውይይት ተካሄደ፡፡ በዚህ ውይይት ላይም የምንሰራው ወንጀል የለምና ምንም ሊያሰጋን የሚገባ ነገር የለም የሚለው ክርክር አንዳለ ቢሆንም እየበረታ ካለው የደህንነቶች ወከባ አንጻር ተረጋግተው አንዲመለሱ ማድረግ የሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ውሳኔ ተሰጠ፡፡ ፡፡ በዚህም መሰረት ጦማሪ ናትናኤል ደህንነት አባሉ በሚያናግረው ወቅት ስራችንን አንዲያስረዳው (  ደህንንቱ ትዊተር ፌስ ቡክ አጠቃቀም አንዲያሳየው ፣ የተጠረዘውን የዞን9 ስራዎች ስብስብ አንዲሰጠው እና ክትትላቸውም አግባብ አንዳልሆነ እንዲገልጽለት) ተወሰነ፡፡ መንግሰት አዲሱ ስጋት ከ ለምን ተናገራችሁ? ወደ ለምን ዝም አላችሁ? የተቀየረ በመሆኑ ዝምታችን ማቆምና የመመለስ ዝግጅት ማድረግ አንደሚገባ፣ እንዲሁም በደህንነቶች በከፍተኛ ሁኔታ ስማቸው የሚነሳ የቡድኑ አባላት ከፍተኛ የደህንነት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አንዲመች የደህንነት ስጋት ቅደም ተከተል በማውጣት ጦማሪት ሶልያና እና ጦማሪ በፍቃዱ በአንደኛ ደረጃ በመንግሰት ደህንነቶች አይን በመታየት ጦማሪ አጥናፍ እና ናትናኤል (ናትናኤል በቀጥታ እያናገሩት በመሆኑ እና አጥናፍ ቀድሞ የሚሰራበት መስሪያ ቤት በመሄድም ጭምር የክትትል ሂደቱ ስለጠነከረበት ) በሁለተኛ ደረጃ  በከፍተኛ የደህንነት ግንኙነት መረብ ውስጥ በመሆን  እነዚህ ጦማርያን አስፈላጊውን ጥንቃቄ አንዲያደርጉ እና ወደፊትም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝም ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ የተለያዩ እርምጃዎችን መውሰድ አንደሚያስፈልግ  ለጊዜው ግን ወደ ተለመደው ኢንተርኔት በመመለስ ምንም እየሰራን አንዳልሆነ ማሳየት አለብን የሚል ውሳኔ ተደረሰ፡፡ ( በወቅቱ ሌሎች ጦማርያን ላይ ያለው ስጋት ተመሳሳይ ደረጃ ላይ ነው የሚል ድምዳሜ ነበር)

በዚሁ ወር መጨረሻ ጦማሪ አቤል ዋበላ ላይ ከምሽቱ 2 ሰአት 22 አካባቢ በፌዴራል ከሚጠበቅ የመንግስት መስሪያ ቤት አጠገብ ከፍተኛ የአካል ድብደባ ደረሰበት በድብደባው ራሱን የሳተ ሲሆን ሲነቃ ከላፕቶፑና ከስማርት ስልኩ ውጨ የተወሰደ ምንም ንብረት አለመኖሩም ሌላ ከፍተኛ ጥርጣሬን አስነሳ፡፡
በዚያው ወር መጨረሻ ጦማሪ ናትናኤል ለደህንነት አባሉ የዞን9 ስራዎችን የሚያሳይ ጥራዝ በመስጠት የአባላቱን የፌስ ቡክ እና የትዊተር አንቅስቃሴ አንዴት መከታተል አንደሚችል በተወሰነው መሰረት አስረዳው፡፡ ከሚታየው ውጪ የምንሰራው ነገር የለም የዝምታችን ምንጭም የደህንነቶች ወከባ መሆኑን ተናገረ ፡፡ በተደጋጋሚ ህጋዊ መታወቂያ ቢጠይቀውም የደህንነት አባሉ መታወቂያ ለማሳየት ፍቃደኛ አልነበረም፡፡ በዚሁ ወር ከቀድሞው በተጨማሪ ከአሁን ታሳሪዎች በአንደኛው ላይ ከደህንነቶች ጋር አብሮ የመስራት ጥያቄው ጠነከረ፡፡ አብሮ ካልሰራ የመታሰር አደጋ አንዳለውም ደጋግመው አስጠነቀቁት፡፡ ነገር ግን ማስፈራሪያውን ተከትሎ የሰሩትን ህገ ወጥ ስራ ስለማላውቅ ልተባበር አልችልም ብሎ በአቋም ጸና፡፡


ሚያዝያ 2006  -የቡድኑ የወቅቱ አስተባባሪ ናትናኤል ፈለቀ አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቶች ጋዜጠኞች እና ጦማርያን የሚያደርጉበት አመታዊ የልምድ ልውውጥ ላይ ለመሳተፍ ወደ ስዊድን ተጉዞ ተመለሰ፡፡ በዚሁ ወር መጀመሪያ ከዞን9 ጦማርያን ጋር ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ጋር ተያያዥ ስራዎችን በመስራት አጋር ድርጅት የሆነው የአርቲክል 19 ሰራተኛ አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ላይ ለ36 ሰአታት ተይዞ ከአገር አንዲወጣ ተደረገ፡፡ በወቅቱም መንግሰት ድርጅቱ የሚሰራውን ስራ አንወደውም ከማለት ውጪ ለማባረሩ የሰጠው ሌላ ምክንያት አልነበረም (ይህ ድርጅት ከዚህ ቀደም አቶ ሽመልስ ከማልን ጨምሮ ለሌሎች ባለስልጣናት ስልጠና የሰጠ ሲሆን የሚዲያ ሕጉ በሚወጣበት ወቅት ከመንግስት ጋር አብሮ ይሰራ የነበረ መሆኑ ይታወሳል )
በዚሁ ወር በነበረው በጄኔቫ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሚካሄደው የኢትዮጲያ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሰባአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ የሀገራት የእርስ በርስ መገማገሚያ ስነ ስረአት ቅድመ ግምገማ (Pre UPR) ሊሳተፉ ተጋብዘው የነበሩ ሁለት ጦማርያን የመንግስትን ክትትል ለማረጋጋት በማሰብ ጉዞአቸውን ሰረዙ ፡፡

በመጀመሪያው ሳምንት በጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ፣ በጦማሪ አጥናፍ ላይ የነበረው ክትትል በመጨመሩ እና በጦማሪ አቤል ላይ የደረሰው ድብደባ አጠራጣሪነቱ ከመጨመሩም በተጨማሪ ሌሎች የዞን9 ወዳጆች ከደህንነቶች በተደረገ ተከታታይ የስልክ ጥሪ ጆማኔክስ እና ማሂፋንትሽ የሚባሉ ጦማርያንን አድራሻ አንደሚያውቁና አንዲናገሩ መጠየቃቸውን ተናገሩ፡፡  
በተመሳሳይ ቀን ከደህንነት ቢሮ ጦማሪ ናትናኤል ጋር ተደውሎ የዘጠኙንም አባላት ሙሉ ስም የስልክ አድራሻ እና የሚሰሩበትን መስሪያ ቤት አንዲገልጽ ተጠየቀ፡፡ ( ናትናኤል በወቅቱ ስራቸውን ለመስራት የተሻለ ስልት መጠቀም አንደሚገባቸው በማሳሰብ የማንንም አድራሻ ለመናገር ፍቃደኛ አንዳልሆነ መለሰ)

በእለቱ  ምሽት በጣም አስጊ የሆኑትን ጉዳዪች አስመልክቶ ከፍተኛ ውጥረት የነገሰበት ውይይት ተካሄደ፡፡ በመሆኑም ዝም በማለት የመንግስት ደህንነቱን ለማረጋጋት የተደረገው ሙከራ አለመሳካቱ አንደውም ለምን ዝም አሉ ወደሚለው መንገድ ማምራቱን ተከትሎ መናገርም ዝም ማለትም ያልተፈቀደልን የቡድኑ አባላት የተለያዩ ምን ማድረግ ይገባል የሚሉ ተከታተይ ውይይቶችን በየቀኑ ማካሄድ ተጀመረ፡፡[በወቅቱ የስጋቱን ከፍተኛ ደረጃ መድረስ ተከትሎ አውሮፓ ቪዛ ያለው ጦማሪ በፍቃዱ ለጊዜው ከአገር ወጥቶ ዞር አንዲል  የቀረበለትን ጥያቄ ውድቅ አደረገው፡፡ ( በወቅቱ በነበረው መረዳት ከፍተኛ አደጋ ላይ አለ ተብሎ የታሰበው በፍቃዱ ነበር)

 ተከታታይ ውይይቶቹ ሲጠናቀቁ ሁለት ሃሳቦች ለውሳኔ ቀረቡ - አንደኛው እየተጠናከረ የመጣውን ጫና በይፋ በመግለጽ ዞን9ን በመበተን ቡድኑ በይፋ እንዲዘጋ ማድረግ ሲሆን ሁለተኛው ደሞ ወደተለመደው የኢንተርኔት  እንቅስቃሴ በመመለስ እስካሁን ቡድኑ የጠፋበትን ምክንያት መግለጽና ተመሳሳይ የሆኑ ክትትሎችን በተከታታይ ለአአደባባይ ማዋል  በሚል ውይይት ተደረገ፡፡ በዚህ ቀናትን በፈጀ ውይይት ለመጀመሪያም ( ምናልባትም ለመጨረሻ ጊዜም) ውሳኔ ለመስጠት ድምጽ ብልጫ ይደረግ በተባለው መሰረት  በአንድ ተቃውሞ በሁለት አብላጫው በወሰነው እስማማለሁ እና በስድስት ድጋፍ ወደእንቅስቃሴ ለመመለስ ተወሰነ፡፡ ተያይዞም ከደህነት የሚመጡ ጥያቄዎቸን ከዚህ በሁዋላ ማስተናገድ አንደማይገባ ተወሰነ፡፡  

( በዚህ ውሳኔ ወቅት ሁሉም ጦማርያን መንግስት በፍጥነት የእስር እርምጃ ይወስዳል የሚል ግምት ያልነበረን ሲሆን ወደስራ ተመልሰን “ተጽእኖ” እስክንፈጥር ወይም የስራችንን ይዘት አይተው እርምጃ ይወስዳሉ በሚል ግምት ከጥቂት ጊዜያት በሁዋላ ሊመጣ የሚችለውን ነገር አና መደረግ የሚገባቸውን ስራዎች ማዘጋጀት ላይ ከማቀድ ውጨ ያደረግነው ዝግጅት አልነበረም፡፡) 


ሚያዝያ 15 - የዞን9 አባላት ሁሉም በተለመደው ሁኔታ የኢንተርኔት እንቅስቃሴያቸን መመለሳቸውን የሚገልጽ መግለጫ ወጣ፡፡ በወቅቱም ለጊዜው የእስረኞች አያያዝን፣ እየተነቃቃ መጣውን የኦሮሞ ብሄርተኝነት ተከትሎ ታዋቂ የኦሮሞ ፓርቲዎች ፕሮግራምን ማስተዋወቅን( ልዩነቶቻቸው እና አንድነቶቻቸውን)  እና ለመጪው ምርጫ የሚሰሩ ዘመቻዎችን ማዘጋጀት ላይ ማተኮር የመመለሻ ስራዎች አቅጣጫ አንዲሆን ተወሰነ፡፡  ተወሰነ፡፡ በተጨማሪም በመጪው ሳምንት የሚካሄደውን የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ በሰባአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ የሀገራት የእርስ በርስ መገማገሚያ ስነ ስረአት አስመልክቶ መረጃዎችን መስጠት ላይ አንድናተኩር እና ቀድመው ታቅደው ነበሩ የዞን9 ስራዎችን መከለስ የመሳሰሉ የስራ ክፍፍሎች ተሰጡ፡፡ 


ሚያዝያ 17 - ሚያዝያ 17 ማምሻውን በተመሳሳይ ሰአት የዞን9 ጦማርን በያሉበት እየተያዙ እነደሆነ መረጃዎች ተሰሙ፡፡ያንን ተከትሎ  እስሩ እየተከናወነ ያለው በተመሳሳይ ሰአት  በመሆኑ መረጃዎች እነደተሰሙ ለሁሉም ጦማርያን ለማስተላለፍ የተደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀረ፡፡ በእለቱ 6 ጦማርያን መያዝ ሲረጋገጥ እስሩ እየተከናወነ እያለ ከመታሰሩ ቀድሞ መረጃ ማድረስ የተቻለው ለጦማሪ ጆማኔከስ በመሆኑ ማምሻውን በአስቸኳይ ነበረበትን ከተማ ቀየረ፡፡


ሚያዝያ 18 - ጦማሪ ጆማኔክስ ካሳየ በተጣደፈ በጣም አጭር የቡድን ውሳኔ ከአገር በፍጥነት ወጣ፡፡ ( ከአገር የወጣው የመጨረሻው ጦማሪ በመሆን ከመንግሰት የተቀናጀ አፈና የተረፈው ብቸኛው የዞኑ ጦማሪ በመሆን ስደትን ተቀላቀለ) በተጨማሪም የዞን 9 ወዳጅ የነበሩ ጋዜጠኞች በተመሳሳይ ክስ መአከላዊ ምርመራ ለእስር አንደተወሰዱ ተሰማ።


 ሚያዝያ 19 - የህግ አማካሪ እና ቤተሰብ ባልተገኘበት እሁድ ቀን አራዳ ፍርድ ቤት ጦማርያኑ ከእስረኛ ጋዜጠኞች ጋር ቀረቡ በወቅቱም ፓሊስ ራሱን የሰብአዊ መብት ተቋም በሚል ከሚጠራ ድርጅት ጋር በመተባበር ህገ መንግሰታዊ ስርአቱን በሃይል ለመናድ በማህበረሰብ ሚዲያ አመጽ የመቀስቀስ ዝግጅት በማድረግ ወንጀል መጠርጠራቸውን መግለጹን ከፍርድ ቤት ፋይሉ መረዳት ተቻለ፡፡
የተባበሩት መንግስታት ክሱን ተከትሎ ከሰብአዊ መብት ተቋማት ጋር መስራትን ወንጀል ማድረግ አደገኛ እና ከአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎች ጋር የሚጋጭ መሆኑን በማሳወቅ አስቸኳይ መግለጫ አወጣ፡፡ ይህንንም ተከትሎ በመቶዎች የሚጠጉ የሰብአዊ መብት ተቋማት እስሩን የሚያወግዙ መግለጫዎችን አወጡ፡። በተመሳሳይ ወር ግሎባል ቮይስስ የመጀመሪያውን አለም አቀፍ የጦማርያኑ እና የጋዜጠኞቹ እስርን የሚቃወም ዘመቻ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን በሺዎች  የሚቆጠሩ በመላው አለም ያሉ የሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ተሟጋቾች አጋርነታቸውን አሳዩ፡፡ በማህበረሰብ ሚዲያዎችም አበረታች የአጋርነት ድጋፎች  ታዩ፡፡


ሚያዝያ 23 እና 24 - ጦማሪ ጆማኔክስ ካሳየ መኖሪያ እና የስራ ቦታ ከፍተኛ ወከባ እና ተያያዥ ጥያቄዎች ለተለያዪ ሰዎች ቀረቡ፡፡ መንግሰት ደህንነት ሰዎች ባደረጉት በዚህ ከበባ የጦማሪውን አገር ውስጥ አለመኖር ተረዱ፡፡

ሚያዝያ 29 እና 30 - የዞን9 ጦማርን እና ጋዜጠኞች ፍርድ ቤት በሚቀርቡበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ በቤተሰብ አና በጓደኞቻቸው መታየት ቻሉ፡፡ ሁለት ጦማርያንም ድበደባ እና ኢሰብዓዊ  የሆነ እንግልት እንደደረሰባቸው ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቀረቡ፡፡ በተመሳሳይ ወር በሁሉም እስረኞች ላይ ከድብደባ ከኢሰብአዊ አያያዝ  የአንቅልፍና የምግብ መክከል አንዲሁም ሌሎች ለአደባባይ የማይገለጹ መንገላታቶች ደረሱባቸው፡፡


 ግንቦት 2006 - በዚህ ወር በአራት የተለያዩ ቀናት በተለያዪ ቡድኖች ወደ ፍርድ ቤት የቀረቡት ጦማርያን እና ጋዜጠኞቹ ክስ ከሰብአዊ መብት ተቋማት ጋር በመስራት አመጽ ማነሳሳት ከሚለው ወደ ሽብተኛነት ጥርጣሬ ተቀየረ፡፡ አዲስ ወንጀል ለመቀየሩ ማእከላዊ ምርመራ ያሳየው ምንም አይነት ማስረጃ ባይኖርም የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮን እንደፈለገ ማግኘት ቻለ፡፡ በዚሁ ወር በነበረው የመጀመሪያ ቀጠሮ ባለፈው አቤቱታ ካቀረቡት በተጨማሪ ጦማሪ አጥናፍ ብርሃኔ በሌሊት እየተጠራ ምርመራ እንደሚደረግበት እና ድብደባ አንደተፈጸመበት ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቀረበ፡፡
በዚሁ ወር ጦማርኑ ከታሰሩ ከአራት ሳምንት በሁዋላ “የሽብር ወንጀል ተጠርጣሪ” በሆነችው በጦማሪ ሶልያና ሽመልስ ቤት በሌለችበት  በሁለት ዙር የተከፈለ ብርበራ ተካሄደ፡፡ በመጀመያው ዙር ምርመራውን ጨርሶ የሄደው ፓሊስ ያልተፈተሹ ቀሪ ቦታዎች አሉ በማለት ፍሪጅ ጀርባ የግንቦት ሰባት ፕሮግራምን አግኝተናል ሚል የክሱን ፓለቲካዊነትና የደህንንት ተቋሙ የደረሰበትን ቅሌት ደረጃ ያመላከተ ማስረጃ ፈጠራ አካሄደ፡፡ በዚያም በተፈጠረ አታካሮ የጦማሪዋ እናት አልፈርምም በማለት የተቃወሙትን ሰነድ ፓሊስ ራሱ ይዞ ባመጣቸው ምስክሮች አስፈርሞ ሄደ፡፡ ብርበራውን አስከትሎ የክሱ አቅጣጫ የተለመደው የሽብርተኛነት የተመደቡ ድርጅቶች ጋር ማያያዝ መሆኑን ብዙዎች ገመቱ፡፡

ሰኔ 2006 - በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት በመመላለስ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀባቸው ጦማርያን እና ጋዜጠኞች በሳምንት ሁለት ቀን ብቻ ከቤተሰብ ጋር እየተገናኙ ከፍርድ ቤት ቀጠሮ አንድ ቀን ቀድሞ ካልሆነ በስተቀር ከጠበቃ ጋር የመመካከር እድላቸው እነደተከላከለ ማእከላዊ ምርመራ ከረሙ፡፡

ሃምሌ 2006- ወራትን የፈጀው ክስ አሳፋሪ ክስ በልደታ 19ኛ ወንጀል ችሎት ተከፈተ፡፡ በማንኛውም ተራ ግለሰብ ዘንድ የሚታወቀውን ሃቅ በማዛባት ሁሉንም የአንድ አሻባሪ ቡድን አባላት በማስመሰል ቀረበው ክስ ከ20 አመት ጀምሮ እስከ ሞት ድረስ የሚደርስ ቅጣትን የሚመለከት ሆኖ ቀረበ፡፡ ዞን9 የሚለውን የቡድኑን ስም አንድም ቦታ ያልጠቀሰው ይህ ክስ ጦማሪት ሶልያና ሽመልስን አንደኛ ተከሳሽ አድርጎ በመጨመር 10 ሰው ላይ የቀረበ ሲሆን ምን አንደሆነ የማይታወቅ ሽብር ተግባር በመጥቀስ የኢንተርኔት ደህንነት ስልጠናን መውሰድን ዋናው የክሱ ጭብጥ አድርጎ በማቅረብ በተለያዩ የጋዜጠኛነት ፕሮግራሞች ላይ የሚሰጠውን እና አለም አቀፍ ታዋቂነት ያተረፈውን የስልጠና አይነት በሽብር በመፈረጅ ኢትዮጲያን ቀዳሚዋ አገር አደረጋት፡፡ ይህንን ተከትሎም በአገር ውስጥም ሆነ አለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ዘንድ ግርምት ተስተዋለ፡፡ በዚሁ ወር ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ወደ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች ተዘዋወሩ፡፡ ጦማሪት ማህሌት እና ጋዜጠኛ ኤዶም በስተቀር የቀሩት ተከሳሾች በጓደኞቻቸው መጠየቅ ቻሉ፡፡


ነሃሴ 2006 - ዘጠኙም ተከሳሾች ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ ለጥቅምት 05 2007 አም ተቀጠሩ፡፡ ከፍተኛው ፍርድ ቤትም በሌለችበት ክሷ የሚታየውን ጦማሪት ሶልያና ሽመልስን መጥታ ክሷን አንድትከታተል በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ አደረገ፡፡

አዲስ ህልም በማለም የተጀመረው አመትም 6 ጦማርያንን 3 ጋዜጠኞችን በማሰር 3 ሌሎች ጦማርያንን ለስደት በመዳረግ ተጠናቀቀ፡፡

ማስታወሻ (ወዳጅ ጋዜጠኞች ከዞን9 ጦማርያን ጋር በመተዋወቃቸው ብቻ ታሰሩ ሲሆን ከጋዜጠኛ ኤዶም በስተቀር በዞን9 ዘመቻዎችም ላይ ተሳትፈው የማያውቁ ጓደኞች ብቻ ነበሩ፡፡ በነበረው ከፍተኛ ወከባ የመታሰር እጣ ሊኖር አንደሚችል ብንገምትም ሶስቱን ጋዜጠኞች አብረው ይታሰራሉ የሚል ግምት ፈጽሞ አልነበረንም ፡፡)

*************************************************************************************************************
ይህንን ከ24- 31 አመት በሚደርሱ ወጣቶች ያገባናል ብለው ሃሳባቸውን በመግለጻቸው ብቻ የደረሰ ግፍ፣እስር፣ እንግልት፣ ስደት እና ለቁምነገር እና ለአገር ደህነት መዋል የነበረበትን  የመንግሰት ከፍተኛ ሃብት እና የሰው ሃይል ወጣት ዜጎችን በመከታተል ማባከን በከፍተኛ ሁኔታ ያሳዝነናል፡፡ በዚያው መጠን ለዚህ መስዋእትነት እየከፈሉ ባሉ ጓደኞቻችን እንኮራለን፡፡ ዞን9 መሰረታዊ የሆነው ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ለማግኘት የሚደረግ ትንሽ ሙከራ ነው፡፡ ይህንነ ሙከራ ያለምንም ማቅማማት በፈጠራ ክስ መምታት ሂደቱን ያስተጓጉለው አንደሆነ አንጂ ጨርሶ አይገለውም ፡፡ ታሪክም ምክንያታዊነትም አንደሚያሳው ይህ አይነቱ የመንግሰት ጭፍን እርምጃ ምሬትን ሲጨምር አንጂ ሊያስቀር አይችልም፡፡ በመሰረቱ ዘጠኝ ወጣቶች የሚሸበር መንግስት ለትችት ለመስማት ያለው ትዕግሰት ዜሮ ሊባል በሚችል ሁኔታ መሆኑ ከዞን9 እስር በላይ ምስክር የለም፡፡ እንደዛ ባይሆን ኖሮ “ህገ መንግስቱ ተከብሮ እያለ ህገ መንግስቱ ይከበር በማለቴ ጥፋተኛ ነኝ” የሚል የጥፋተኛነት ቃል በማስፈረም ባልቀለደ ነበር፡፡ 

በመጨረሻም እስር ቤት ለሚገኙ ጓደኞቻችን እና ያልተገደበ አጋርነታቸውን ላሳዩ የዞን9 ነዋሪያን ከልብ የመነጨ የመልካም አዲስ አመት ምኞት እናስተላልፋለን፡፡ጓደኞቻችን እስር ቤት ውስጥ ሆነው የሚቀበሉት አመትም ህልማቸውን የገደበ ቢሆንም በጽናትና በኩራት እነደሚወጡትም ሙሉ እምነታችን ነው ፡፡ በመሰረቱ ወንጀል ያልሰራ እና በፓለቲካ ልዩነት ብቻ የተከሰሰ ህሊና አንገቱን የሚያስደፋው ምንም ምክንያት አይኖርም፡፡ በስደት የምንገኝ ጓደኞቻቸውም እስራቸውንና እንግልታቸውን ልባችንን ቢሰብረውም አንገታችንን በኩራት ቀና የምናደርግበት እና እስራቸው ትርጉም የለሽ የማይሆነበት አመት እንደሚሆን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ሃሳብን መግለጽ የሚደረግ ጥረትና ትግል ከሚመጡበት ተግዳሮቶች በመነሳት አቅጣጫ ይቀይር ይሆናል አንጂ አይቋረጥም የዞን9ኛውያን ጥረትም ከዚያ የተለየ አይሆንም፡፡

ስለሚያገባን እንጦምራለን!
Zone9 Bloggers and Journalists Pic edited by Fractal Element