Sunday, July 29, 2012

ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ - ስምንት


(ከሐምሌ 16 እስከ ሐምሌ 22፤ 2004)

Capital ጋዜጣ ‹‹Counting 20›› በሚል ርዕስ ባስነበበው የሽፋን ገጽ ታሪክ ላይ አቡነ ጳውሎስ የጵጵስና ‹‹ስልጣን›› የያዙበትን 20ኛ ዓመት አከባበር ይተርካል፡፡ በዓሉ በሸራተን አዲስ ሆቴል ሲከበር የተለያዩ ሃይማኖት አባቶች፣ የቢዝነስ ሰዎች እና የፖለቲካ ሰዎች ተገኝተዋል - ከነርሱም ውስጥ ቴዎድሮስ አድሃኖም እና ኃ/ማርያም ደሳለኝ ይገኙበታል፡፡

** ** **

Fortune  ጋዜጣ “Fineline” በተሰኘው የሚስጥር አምዱ ላይ ሰማሁ ብሎ ካንሾካሾካቸው ምስጢሮቹ ውስጥ መለስ ጁላይ 20 አዲስ አበባ ስለመግባታቸው፣ በርሳቸው ስም ተፈርመው የወጡ ዶክመንቶች ስለመኖራቸው እና እረፍታቸው ለአንድ ሳምንት ያህል የሚቀጥል መሆኑን ተናግሯል፡፡

** ** **

አዲስጉዳይ መጽሔት ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ ከፖለቲካ ሳይንስና የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ገብሩ ታረቀ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ ይዞ ወጥቷል፡፡ ከቃለምልልሱ ውስጥ የተቀነጨበውን እነሆ፡-

‹‹…በእኔ አስተያየት ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ተቃዋሚ ፓርቲዎች አሉ ብሎ ለመናገር ያስቸግራል፡፡ ድምጻቸው ጠፍቷል፡፡ አይታዩም፡፡ ግን አለን ይላሉ፡፡››

‹‹…እኛን ከሶቪየት ህብረትና ከዩጎዝላቪያ ጋር ማወዳደር ግድ ይሆንብኛል፡፡ በሁለቱም አገሮች የፌዴራል ስርዓቱ የተሳሰረው ከአውራው ፓርቲና ከአንድ ግለሰብ መሪ አውራነት ጋር ነበር፡፡ ሁሉቱም (ፓርቲውም አውራ መሪውም) ከስልጣን ሲወገዱ በሁለቱም አገሮች ፌዴሬሽኑ ፈራረሰ፡፡…››

‹‹…ሙስና ለእኔ ዋናው በሽታ ሳይሆን የበሽታው አንድ ምልክት ነው፡፡ ችግሩ (በሽታው) የዲሞክራሲና መልካም አስተዳደር መምከን፣ ስልጣን በአንድ ፓርቲ መዳፍ ውስጥ መግባት ነው፡፡››

‹‹…ህዝቡ በፍርሃትና በተለያዩ ምክንያቶች ዝም ሲል እንደተስማማ አድርጎ መቁጠር ስህተት ነው፡፡ ከሚጮህ ዝም ያለ ሕዝብ አደገኛ ነው፡፡…››


ሌላም ሌላም
ርዕሰ አንቀጾች
የሳምንቱ ጥቅስ
       ‹‹አጠገቡ ካሉ ሰዎች እንደምሰማው ጤንነቱ በፍጥነት እየተሻሻለ ነው፡፡››
አቦይ ስብሓት ነጋ ለአዲስ አድማስ 
ጋዜጣ ስለመለስ ጤንነት ከተናገሩት!

No comments:

Post a Comment