Wednesday, November 28, 2012

የሰሞኑ ጦማሮች እፍታ


ማሕሌት ፋንታሁን

በኢትዮጵያ የሚገኙ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች ቁጥር በባለፈው ዓመት 246,360 የነበረው በአሁኑ ዓመት በአስገራሚ ፍጥነት 839,580 መድረሱንና ነገር ግን ካለን የሕዝብ ብዛት ሲነፃፀር 0.95 ፐርሰንት ያክሉ ብቻ ተጠቃሚ እንደሆነና ከዚህም ውስጥ የገዢው ፓርቲ ቤተሰቦችና ደጋፊዎች እንደሚበዙ - ከሌሎች ሃገራት ጋር በማነፃፀር ያስነበበን ኢትዬ ቼንጅ የተሰኘ ጦማር ነው፡፡ ሙሉው እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

አብዪአዲ የሚገኘውና በጀግናው ራስ አሉላ አባነጋ ስም ተሰይሞ የቆየው የሁለተኛ ደረጃ /ቤት ስያሜው ተቀይሮ በመለስ ዜናዊ ስም እንዲሰየም መወሰኑን ታማኝ ምንጮች ማስታወቃቸውን የገለፀው ይኸው ኢትዮ ቼንጅ ጦማር ሲሆን የተጻፈው በኢየሩሳሌም ስዩም ነው፡፡ “በደርግ ዘመን የተሰራውና በራስ አሉላ ስም ተሰይሞ 9-10 ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር ከቆየ በኋላ 2002 . ጀምሮ የት/ቤቱን አቅም ለማሳደግ በሚል 11-12 መማሪያ ክፍሎችን ለመገንባት በአገር ውስጥና በውጭ አገራት የሚገኙ የአካባቢው ተወላጆች ገንዘብ አዋጥተው ሥራው መከናወኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። ግንባታው ተጠናቆ ባለፈው ነሐሴ ወር ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ እንዳለ አቶ መለስ በማለፋቸው ፕሮግራሙ መሰረዙን ሲታወቅከሁለት ሳምንት በፊት በተከናወነው የምረቃ ሥነ-ስርአት የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት በስፍራው እንደተገኙ ማወቅ ተችሎዋል።” ሙሉው እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ይሄው ጦማር ባሳለፍነው እሁድ ኅዳር 16/2005ዓ.ምን አንድነት ፓርቲ አዘጋጅቶት በነበረው ፕሮግራም ላይ የውይይቱ አቅራቢ እና የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ‹የወቅቱ የአገራችን የፖለቲካ ሁኔታና የወደፊት የትግል አቅጣጫ› በሚል አርዕስት ያቀረቡትን ጽሑፍም አስነብቦናል፡፡ ሙሉው እዚህ ላይ ታገኙታላችሁ፡፡


ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ ሁለት የሃገራችን ከፍተኛ የጦር አመራሮች፤ የመከላከያ ሚኒስቴሩ አቶ ሲራጅ ፋጌሳ እና ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ኢንቨስትመንትን ለማስተዋወቅ በሚል ምክንያት መሄዳቸውን በተመለከተ መግለጫ ሳይሰጥ ዋሽንግተን ዲሲ እንደሚገኙ የሚያወራው ኢትዮ ሴንተር ጦማር ነው፡፡ ሙሉው እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

“ለሕሊና እስረኞች የሚሟገተው ፍሪደም ናው (‘Freedom Now’) የሚባለው ድርጅት የእስክንድር ነጋን ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላግባብ የታሠሩ ሰዎችን ጉዳይ ለሚያጠናው ግብረኃይል ማቅረቡ ታወቀ።” የሚለን ፊንፊኔ የተሰኘ ጦማር ነው፡፡ በተጨማሪም ግብረ ኃይሉ በቀረበለት መመልከቻ ላይ በመጭው ሚያዝያ ውሣኔ እንደሚሰጥ እንደሚጠበቅም ገልጧል።

የመጨረሻዎቹ ቤተ እስራኤላውያን ወደ እስራኤል ለመጓዝ ተዘጋጅተዋል::130,000 ኢትዮጵያውያን ይሁዲዎች ወደ እስራኤል ይበራሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው:: በማርች 2014 ይጠናቀቃል ተብሎ የታቀደው ይህ ኦፕሬሽን የኢትዮጵያ የጥንት ታሪክ ምዕራፍ መዝጊያ ተደርጎ ታስቧል::” የሚለን ደግሞ የሚኒሊክ ሳልሳዊ ጦማር ነው፡፡ AFPን ጠቅሶ ያቀረበውን ሙሉ መረጃ እዚህ ላይ ያገኙታል፡፡

እዚህ የዞን ዘጠኝ ጦማር ላይ ደግሞ በፍቃዱ ኃይሉ የመቀሌ የአንድ ቀን ቆይታውን ‹የጉዞ ማስታወሻ፤ መቐለን በአንድ ቀን› በሚል ርዕስ ያስነበበን ሲሆን ስለ መቐሌ ከተማዋና ዝቦቿ፣ የአፄ ዮሓንስ ቤተ መንግሥት፣ የሰማዕታት መታሰቢያ እና ሙዚየም በአንድ ቀን እንደታዘበው ያቀረረበበት ነው፡፡ ሙሉውን እዚህ ላይ ታገኙታላችሁ፡፡

No comments:

Post a Comment