Saturday, May 28, 2016

የግንቦት 20 ፍሬዎች




ቤተል ፋንታሁን የ25 ዓመት ወጣት ስትሆን፣ በኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ዘመን ተወልዳ ያደገች ነች፡፡ በሌላ አነጋገር አንዳንዶቹ ‘The EPRDF Generation’ የሚሉት ትውልድ አባል ናት፡፡ ቤተል ብቻ ሳትሆን ስልሳ አምስት በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ወዲህ የተወለዱ ሲሆን፣ ይሄም ከአገሪቱ አጠቃላይ ሕዝብ ሁለት ሦስተኛውን ይሸፍናል፡፡ ቤተል በዚህ ዕድሜዋ “እውነተኛው የግንቦት 20 ፍሬ ግንቦት 7 ብቻ ነው፤ ሌላው ሁሉ ግንቦት 20 ቢኖርም ባይኖርም መኖሩ አይቀርም” ትለናለች፡፡ አንብቧት፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ)ን 6 ወራት ዕድሜ አንሰዋለሁ፤
ድንገት ቸኩሎ ገብቶ ነው እንጂ ይደርስብኝ ነበር። እኔ ተረግዤ  የጎተራው ሼል ይሁን ተቀጣጣይ ነገር (ግንቦት 27፣ 1983) ፈንድቶ ሕዝቤ ሸሽቶ እኛ ሰፈር መጣ አሉ፡፡ ታዲያ አንዳንዶች ሲያሾፉብንየዛኔ ጥለውሽ ነው ያገኘንሽ ብለው ያወራሉ”፡፡ የኛን ሰፈር እወደዋለሁ፡፡ ግንቦት 20 ከሚባለው 2 ደረጃ ትምህርት ቤት ውጪ ኢሕአዴግ ለኛ ሰፈር ያደረገው ነገር የለም፡፡  ምህርት ቤቱም፣ ሰፈሩም በ97 ምርጫ ማግስት በተያዘብን ቂም ምክንያት 50 ዓመታት በላይ ያሳለፈ ሰፈር ባለፈው ዓመት ነውኮብልሰቶን› የገባበት፡፡ እንዲያውም ከአንዳንድ ሰዎች ጋር ተማክሬ UNESCO ላይ ለስመዘግበው ስል ለጥቂት ነው የቀደሙኝ። እሱ ይገርማችሁዋል፡፡ የቀድሞው የኢሕአዴግ ጠቅላይ ሚኒስትርየመረሸ› ጊዜ እንኳን ብቸኛው ድንኳን ያልተጣለበት ሰፈር ነው፤ የኛ ሰፈር፡፡ ይሄን ሰማን ብለው ደግሞ የያኔውን ዛሬ እንዳይመጡ።ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” ትሉኝ ይሆናል፡፡ አዎ እዚሁ አዲስ አበባ፡፡

የግንቦት 20 ፍሬ፡ 1

ምርጫ ‘97, ‘02, ‘07

1997 - እንደዛኔ 18 ዓመቴ እንዲሆን የተመኘሁበት ጊዜ የለም:: የዛኔ 8 ክፍል ሚኒስትሪ ተፈታኝ ነበርኩ:: በላያችን ላይ የተኩስ እሩምታ ሲወርድአንፈተንም› ብለን ፈተናው 30 ደቂቃ ዘገየ። እንዲህ እንዲህ እያልን 1998 ላይ ሁለቴ ምህርት ቤቱን አዘጋነው፡፡ በሁለተኛው በፌደራል ተገረፍን፡፡ ሰፈሬን የምወድበት አንዱ ምክንያት የሰፈሬ ልጆች ያኔ ‹ልጆቹን አናስነካም› ብለው ለፖሊሶቹ መንገድ መዝጋታቸውን ሳስበው ነው፡፡ የዛኔ ቤት ሲፈተሽ ኮርኒስ አልቀራቸውም።ወንድ አይትረፍ› የተባለ ይመስል የሰፈሬ ወንዶች ሁሉ ተለቅመው እስር ቤት ገቡ። 2002 ሞራላችን ዝቅ አለ፤ አሽቆለቆለ ሁለት ጣት የልለ፣ አምስት ጣት የለ፡፡ 2007 መቶ ፐርሰንት በልሉን፡፡ ለነገሩ ምርጫ አልነበረም ማለት ነው እኮ፡፡ ፓርላማው ውስጥ  ራሱ ምን እንደሚያደርጉ አላውቅም ልላችሁ ነበር፤ ግን ሳስታውሰው ለካስቤርጎ› ሆኗል፡፡ ዕድሜ ለፌስቡክ ይሁን።

የግንቦት 20 ፍሬ፡ 2

“አንድ ፓርቲ ገዢ ሆኖ አገር ሲመራ ማድረግ ያለባቸው 10 ነጥቦችብዬ ለመዘርዘር አሰብኩና 10 ነጥቦችን ደረደርኩ ለካስ ብዙ ነገር ተደርጎልናል መንገድ፣ ኮንዶሚንየም (ሊያውም ምትሃተኛ)፣ ባቡር ከነመንገዱ:: ግን መንግሥት ይህን ካልሠራ ታዲያ ምን ሊያደርግ ነው? መቼም ከኔ ጋር ቁጭ ብሎቃና› ቴሌቪዥንን አያይ። መንገድ ተሠራ እልልታ፡፡ ቤት ተሠራ እልልታ፡፡ ቆይ ልጠይቃችሁ አለቃ ወይ አስተማሪ አላችሁ እንበል፣ የሆነ ሥራ ተሰጣችሁ፣ ካልሠራችሁ ትባረራላችሁ፡፡ አለቀ በቃ፡፡ ኢሕአዴግም እንዳናባርረው ነው የሚሠራው እሱንም ሠራ ከተባለ (ሽርሽር እንሂድ ብለው ጓሮ እንደሚያዞሩት ሕፃን) የምር ለኛ አስቦ የሚመስለው ሰው ካለ እንተዋወቅ።

የግንቦት 20 ፍሬ፡ 3

ግንቦት 7 ወሳኝ ከምንላቸው የግንቦት 20 ፍሬዎች መሐል ግንቦት 7 አንዱ ነው፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ ከላይ የጠቀስኳቸው ነገሮች በሙሉ ግንቦት 20 ባይኖርም የሚኖሩ ናቸው፡፡ አያጠራጥርም አሁን ሳስበውግንለማለት ካልሆነ በቀርየሚለውን ቃል ራሱ የምንጠቀምበት አይመስለኝም። በኢሕአዴግ ፓርላማ ግንቦት 7 አሸባሪ ተብሎ ከታወጀ በኋላ ብዙ ጓደኞቻችን ከሱ ጋር ግንኙነት አላችሁ ተብለው ተሰቃይተዋል፤ ወኅኒ ወርደወል፡፡ እኛም ከፖሊሶች ጋር አፍ ተካፍተናል። እንዲያውምመቃወም› ለሚለው የአማርኛ መዝገበ ቃል ፍቺአሸበረ› ወይምግንቦት 7› ሊባል ነው የሚሉ ሁሉ አሉ።አሉ› ነው እንግዲህ፤ ያየ የለም፣ ማስረጃ አምጡ እንዳትሉ።

የግንቦት 20 ፍሬ፡ 4

የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ… መቶ ጊዜ ሥሙን መጥራት ሰለቸኝ፡፡ አዋጁን ሳስብ አዋጅ ሳይሆን የግል ሐሳብ ይሆንብኛል። የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ የታወጀበት ዓላማ ለኔ ግልጽ አይደለም፡፡ የአዋጁ ሰለባ ከሆኑት ውስጥ አንዷ እህቴ ነች፤ ለስንት ዓመታት አብራኝ የኖረች እህቴን አይደለም አገር ልታምስ፣ እኔን ነክታኝ የማታውቅን ልጅአሸባሪ› ብሎ መፈረጅ (ለሁሉም የ‹አሸባሪ› ቤተሰቦች) ከባድ ነው። ምን አለ መሰላችሁ? ሌብነትን የማውቀው ሌባ ከሆንኩ  ብቻ ነው፡፡ ሌባ እንዳይሰርቀኝ ብዬ ከተናካሽ ውሻ እስከ አደገኛ አጥር ድረስ ራሴን እከላከላለሁ። የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉም ያው እንደተናካሽ ውሻ የምትፈልገው ሰው ሲመጣ ታስረዋለህ ወይ በተቃራኒው ታስነክስበታለህ። 

ቀጣይ ስንት ግንቦት 20 እንደምናከብር ባላውቅም፤ እኔ ግን ስንትም ባናከብር ደስ ይለኛል፡፡ኢሕአዴግ ግንዴሞክራሲያዊ ነኝ› የሚል ከሆነ ለምን እኛ የመረጥነውን ቀን የድልና የነጻነት ቀን አድርጎ አያከብርልንም?”  የሚል ነገር አሰብኩና ብዙም አልቀጠልኩበትም፡፡ እሺዴሞክራሲያዊ ነኝ› ብሎየብዝኃነት…” ምናምን ብሎ ይጽፋል:: እኔስ ደስ ያለኝን በቀይ ቀለም ማሳለጫው ላይ ብጽፍ ምን አለበት? ምንም! ምናለበት ትውት ቢያደርገን? ውስጣችንን እርም እርም ባያሰኘው።

ማስታወሻ

ማዕከላዊ በአንድ ወቅት አንዱ መርማሪፖለቲካ ላንቺ ምንድነው?” አለኝ፤ የዛኔ ስላልገባኝፖለቲካ አይገባኝም” አልኩት አሁን የተረዳሁት ለሱ ፖለቲካ ኢሕአዴግ ነው፡፡ ኢሕአዴግም ሆነ ግንቦት 20 ለኔ ምኔም አይደለም። “የግንቦት 20 ፍሬዎች” ለኔ ተራ መዝሙር ነው፡፡

2 comments:

  1. You completed a number of fine points there.

    ReplyDelete
  2. I did a search on the subject and found mainly people will agree with your blog.

    ReplyDelete