Wednesday, October 21, 2015

በፍቃዱ ኃይሉ በዋስ እንዲወጣ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስተላለፈ

ዛሬ በልደታ ፍርድ ቤት 19 ወንጀል ችሎት የበፍቃዱን ኃይሉን የአመጽ የማነሳሳት ክስ ዋስትና መብት አስመልክቶ ባስቻለው አጭር ችሎት ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ የዋስትና መብቱ ተጠብቆ በውጪ ሆኖ አንዲከላከል ወስኗል ፡፡ በዚህ መሰረት 20,000 ብር ዋስትና እና ከአገር እንዳይወጣ እገዳ ተጥሎበታል፡፡ ለጥቅምት 27 ተለዋጭ ቀጠሮ የተሰጠ ሲሆን በቀጠሮው በፍቃዱ መከላከያውን ያቀርባል ፡፡ በፍቃዱ የዋስትና ሂደቱን አጠናቆ በእለቱ ከእስር ወጥቷል፡፡

በተያያዘ ዜና አቃቤ ህግ 19 ወንጀል ችሎቱን ውሳኔ በመቃወም ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማለቱ ተሰምቷል።

No comments:

Post a Comment