Thursday, October 8, 2015

ጦማርያኑ ለውሳኔ በድጋሚ ለጥቅምት 5/2008 ዓ/ም ተቀጠሩ

በዛሬው ዕለት በነሶልያና የክስ መዝገብ በዞን ዘጠኝ ጦማርያን ላይ ማለትም በሶልያና ሽመልስ በሌለችበት፣ አቤል ዋበላ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና በፍቃዱ ኃይሉ ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ችሎት ዳኞች አዳማ ስልጠና ላይ ናቸው በሚል ባለመገኘታቸው ምክንያት ለጥቅምት 5/2008 ዓ/ም ቀጠሮ መሰጠቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በእስር 531ኛ ቀናቸውን እያሳለፉ የሚገኙት ጦማርያኑ ይህ የፍርድ ቤት ቀጠሮአቸው ለ38ኛ ጊዜ የተሰጣቸው ነው ፣ ጥፋተኛ ናቸው ወይም አይደሉም የሚለውን ውሳኔ ለማሰማት ፍርድ ቤት የዛሬውን ጨምሮ ለ5ኛ ጊዜ የተሰጠ ቀጠሮ ነው፡፡

ስሜት የማይሰጡ ክሶች እና የተራዘሙ የፍርድ ሂደቶች ዜጎችን በአገራቸው የበለጠ ተስፋ እንዲቆርጡ የሚያደርጋቸው ከመሆኑም በላይ ያለዋስትና በፍርሃት እንዲኖሩ የሚያደርግ ነው፣ ይህ እንዲሆን ካልተፈለገ በቀር በቀጠሮዎች መራዘም ንጹሃንን ጥፋተኛ ማድረግ አይቻልም፡፡

ባልተፈጸመ ወንጀል፣ ባልቀረበ ማስረጃ ዜጎችን ማንገላታት ይቁም፡፡


No comments:

Post a Comment