Wednesday, May 13, 2015

ሶስተኛ አመት

‪#‎Ethiopia‬ #FreeZone9Bloggers 
ለተሻለች ኢትዮጵያ የተሰባሰቡ ያገባናል ያሉ ወጣቶች ከተሰባሰብን ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ጦማራችንን በይፋ ካወጅን ዛሬ ድፍን ሶስተኛ አመታችን ሆነ፡፡
እንደ ዜጋም፣ እንደ አገርም ያለመታደል ሆኖ ብዙ ብለን ተባብለን፣ የምንማማርበት ጊዜ እንዲኖረን አምባገነኖች አልፈቀዱምና ፣ የጠበበው ነጻነት ተዳፍኖብን ሥራችንን ሳይሆን እስራችንን መቁጠር ከጀመርን ደሞ አንድ ዓመት ሞላን፡፡ ራሳችንን እና የተቋቋምንበትን ስራችንን ረስተን እስራችንን ብቻ በምናስብበት ሰዓት ጎግል ልደታችንን ስላስታወሰን እናመሰግናለን፡፡
ይህ ሶስተኛ አመት በእስርና በስደት ያለን ዞን9ኛውያን ሳንነጋገር የምናስታውሰውና ወደኋላ ተመልሰን ሃሳባችንን የምናንጸባርቅበት አንደሆነ እናምናለን፡፡
ሶስቱን አመታት በሙከራችን በጥረታችን እንዲሁም በክፉ ጊዜያት አብራችን ስለቆያችሁ እናመሰግናለን፡፡
አጋርነታችሁ አይለየን ፣ ስለሚያገባን እንጦምራለን፡፡

No comments:

Post a Comment