Wednesday, May 20, 2015

ግልጽ ደብዳቤ ለፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ ከየሸዋስ አሰፋ ቅሊንጦ

ክቡር ፕሬዘዳንት ለመጀመሪያ ጊዜ በቴሌቪዥን ያየሁዎትበፕሬዘዳንትነት ለመመረጥ በተወዳደሩባቸው ጊዜያት ሲሆን በወቅቱ ከእርስዎ ምርጫ ጋር በተገናኘ ድምጽ መስጠት ባልችልም ምርጫውንለመከታተል ብዙ ጊዜዬን እነዳሳለፍኩ አስታውሳለሁ፡፡ በወቅቱ ይህንንያደረኩት የተመረጡት ለአሜሪካን መሆኑን አጥቼው ሳይሆን የታላቅዋ አገር መሆንዎ በወቅቱ ከነበረው ተስፋ ጋር ተደምሮ ለአለም ሰላምሊያበረክቱ የሚችሉትን በጎ ምግባር ተስፋ በማድረግ ነበር ፡፡
አሁን ይህንን ደብዳቤ እንድጽፍልዎት ያነሳሳኝግን ዛሬ መንግሰትዎ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰራተኛ እና የመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ምክትክ ሚኒስትሯ ዌንዲ ሸርማንአዲስ አበባ መጥተው የተናገሩት ንግግር ነው ፡፡ መቼም አንደሚገምቱትአንደማንኛውም ኢትዮጲያዊ ንግግራቸው ስሜቴን መርዞታል፡፡
ምክትል ሚኒስትሯ የተናገሩት ብዙ ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ስለሽብርተኛነት ፣ ስለምስራቅ አፍሪካ ሰላም፣ ስለግንቦት 7 ስለ ኢትዬጵያ እድገት ሰላም ዴሞክራሲ ወዘተ፡፡ ዋና ጉዳይ ብለውየገለጹት የቀጣዩ የ2007 ምርጫ ላይ የሰጡት አስተያየት ግን እጅጉንአሳዝኖኛል፡፡ ምርጫው ከጊዜ ወደጊዜ እየተሻሻለ ነው መጪው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው እንደሚሆን አንጠብቃለን ነበር ያሉት፡፡ ይበልጥ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ የልእለ ሃያልዋ አሜሪካ አቋምመሆኑን መግለጻቸው ነው ፡፡ መቼም በፍቃደኝነት ካልሆነ በስተቀር ምንም አይነት አጭበርባሪ አምባገነን በዚህ ደረጃ ያጃጅላቸዋልብሎ ማመን ይከብዳል፡፡
ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችበመዘርዘር ውድ ጊዜዎን አላጠፋም፡፡ ነገር ግን በኢትዮጵያ በየአምስት አመቱ ምርጫ በመጣ ቁጥር የሚሰሩና እየተሰሩ ያሉ ምርጫ አደናቃፌዎችንልገልጽልዎት እፈልጋለሁ፡፡ ከእነዚህ አደናቃፌዎች መካከል መጨውን ምርጫ 2007 ከመቼውም ጊዜ በላይ የከፋ የሚያደርጉት
1. ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከመዋቅሩ ውጪ ባሉ ግለሰቦች የሚሽከረከር አቅመቢስ ተቋም ከመሆኑም ባሻገርዛሬ ገዥው ቡድን አንደራሱ የፓርቲ አካል የሚያሽከረከረው መሆኑ
2. ገዥው ቡድንም ምንም አይነትየፓርቲ ቅርጽ የሌለውና ከ20 አመታት በፌት ጀምሮ በአሜሪካን መንግሰት በአሸባሪነት ተፈርጆ የነበረው ህወሃት በጠርናፌነት ጠቅልሎየያዘውና ምርጫውንም የስልጣን ጊዜውን ለማራዘም ብቻ የሚጠቀምበትመሆኑ
3. ምርጫ በመጣ ቁጥር 1987ኦነግን ፣ በ1992 መአህድን፣ በ1997 ቅንጅትን ፣ በ2002 አንድነትን በ2007 ሰማያዊን ኢላማ በማድረግ የተሻሉ ተፎካካሪፓርቲዎቸን በማጥፋት አመራርና አባላቶቸን በማሰር ብቻውን የሚወዳደር መሆኑ
4. በፓርቲና በመንግሰት መካከልያለው ልዬነት ጭራሽ ጠፍቶ የፍትህ አካላትና ፍርድ ቤቶቸን ሳይቀር በቀጥታ የፓርቲ አገልጋዮች ያደረገ መሆኑ
5. ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሁኔታዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም የግል ሚዲያ የሌለ መሆኑና 90 ሚሊዬን ህዝብ በሚኖርበት አገር 2000 ኮፒ የሚያሳትሙ ህትመቶችን ሳይቀርበመዝጋት ጋዜጠኞችና ጦማርያንን ወህኒ የከተተ መሆኑ
6. ከምርጫ 97 በኋላ በወጣውአፋኝ አዋጅ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ምንም አንዳይሰሩ ተደርገው ትውልዱ መሪ እና አስተማሪ ያጣ መሆኑ
7. ህገ መንግስቱ ን በጸረ ሽብርአዋጅ በመጣስ የተለያዬ የአገሪቱን ዜጎች በተለይ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኢትዮጲያውያንን በጅምላ ማሰር ፣ በሃይማኖት ጣልቃ መግባት በተለይየእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያንን በጅምላ በማሰር እስርቤቶችን በፓለቲካ እስረኛ የሞላቸው በመሆኑ
8. በአገዛዙ በተለያዬ የስልጣንእርከን ያሉ ግለሰቦች ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ ከልክ ያለፈ ገንዘብ እየመነዘሩና ሙስና ውስጥ የተዘፈቁ በመሆኑ እና ዛሬም በአልጠግብባይነት በዚሁ መቀጠል የሚፈልጉ መሆኑ
9. ምርጫ 2007 የአውሮፓ ህብረትንጨምሮ ሌሎች ተአማኒነት ያላቸውና አምባገነኖችን የማጋለትጥ ልምድ ያላቸው ድርጅቶች የማይታዘቡት መሆኑ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ፕሬዘዳንት ኦባማ-በዛሬዋ ኢትዮጵያ እነዚህ ችግሮች አይኑን ለጨፈነ አንኳን የሚዳሰሱ ሃቆች ሆነው ሳለ የመረጃ ሰዎችዎ ይስቷቸዋል ብዬ አላምንም፡፡ የገዥዎችፕሮፓጋንዳ ስክሪን ሴቨር ኑሮ የሚገለጸውን እውነታም የሚሸፍንባችሁ አይመስለኝም፡፡ ታዲያ ከላይ የተገለጹት መባባሶች መሻሻል ተብለውሲገለጹ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ምን የሚሰማው ይመስልዎታል? ይህ የተገለጸው ደግሞ በዴሞክራሲ በተመረጠ መንግስትና መሪ ካለበት አገርሲሆንና ገዥው ቡድን ለሚደርገው ግፍና ጭቆና አሜሪካ እውቅና ስትሰጥስ ?
እነደሃያል አገር ሲሆንሲሆን የነጻነት ትግል ላይ ያሉ ህዝቦችን ማገዝ ሲገባ ፣ ማገዝ ካልተቻለም ደሞ ቁስላቸው ላይ ሚጥሚጣ ባለመጨመር ዝም ማለት አይቻልም?የአለምን ሰላም ካለነጻነት ማሰብ አንደማይቻል የተቀመጡበት የአባቶችዎም ዙፋን አንደሚያሳይዎት አውቃለሁ ታዲያ የህዝቦችን የነጻነት ትግል ማጣጣል ለምን ??
እርስዎም ሆኑ ሸርማንየአሜሪካንን ጥቅም አንደምታስቀድሙ እናውቃለን፡፡ መረሳት የሌለበት ቁም ነገር ግን ህዝባዊ ወዳጅነትን አንጂ አምባገነን አገዛዙንበመተማመን የሚገኘው ጥቅም ዘላቂ አለመሆኑ ነው፡። ከአገዛዞች ጋር የሚደረገው ቁማር አሜሪካን ቆምኩለት የምትለውን የሞራል ልእልናእና እሴት የሚመጥን አይመስለኝም፡፡ ቢያንስ በአገር ደረጃ ጥቅም ህሊናን ገርስሶ የፓለቲካ ትርፍ ሰው መሆንን ጨርሶ መደምሰስ የለበትም፡፡ትልቅነት የአለምን ሰላም መጠበቅ ከሚወሰድ ሃላፌነት ቀርቶ ሌላውን ለመዋጥ ለሚከፈት አፍ ከተለካ ህገ አራዊት የአለም ትልቁመተዳደሪያ ይሆናል፡፡
ፕሬዘዳንት ኦባማ-ለዴሞክራሲያዊ ስርአት አንጂ ለአምባገነንነት ጥሩ ፊት አንደማይኖርዎት እረዳለሁ፡፡ በአሁኑ መልእክት ግራ የተጋባሁትም ከዚህ የተነሳነው፡፡ አምባገነን የሚያስበው በአይኑ ነው እንደሚባለው የኢትዮጵያ አገዛዝ በአሁኑ ሰአት እውነት ቢነገረውም እንደማይሰማ ይታወቃል፡፡የወይዘሮዌንዲ ሸርማን መግለጫ ሊወድቅ ሳምንታት ሲቀሩት የግብጽ አገዛዝ “strong and stable government” ….. “ጠንካራ እና የተረጋጋ መንግስት” ከሚለው በወቅቱ የአሜሪካንየውጪ ጉዳይ ሚኒስተር ከነበሩት ወ/ሮ ሂላሪ ክሊንተን መግለጫ ጋር ተመሳሳይ ሆኖብኛል፡፡ ይህ አይነት ከእውነታው ያፈነገጠ አገላለጽለሁለቱም አገሮች አንደማይጠቅም ይገባዎታልም ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ፕሬዘዳንት ኦባማ- የኢትዬጵያ ታላቅነት ይመለሳል፡፡ በእርግጥም በነጻነትና በዴሞክራሲ ምርጫ ወደስልጣን የሚወጣ ተርሙን ሲጨርስ ለቀጣዬ በሰላምየሚያስረክብ መሪ ይኖራታል፡፡ ህዝቦቿ በእርቅ ይተቃቀፋሉ፡፡ ጨቋኝም ተጨቋኝም ነጻ ይወጣሉ ፡፡ ኢትዬጵያ ጦር በመስበቅ ሳይሆንፍቅርን በተግባር በመስበክ ለአካባቢዋም ለአለምም አስተዋእጾ የምታበረክትበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም ፡፡ ለዚህ ታላቅ ሽግግር እርሶምአንደመሪ አገርዎም እነደሃያል አገር ከኢትዮጲያ ጎን ብትቆሙ የሁለቱ አገሮች ጥቅም በአለት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡
ቀሪው የስራ ዘመንዎምይህን የአሜሪካን የሞራል ልእልና በተግባር የሚያሳዩበት አንዲሆን እመኝልዎታለሁ፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያንም አሜሪካንንም ይባርክ፡፡
የሸዋስ አሰፋ! ከቅሊንጦኢትዮጵያ

No comments:

Post a Comment