Wednesday, October 5, 2016

የዞን ዘጠኝ ጦማሪው ናትናኤል ፈለቀ ታሰረ


የዞን ዘጠኝ ጦማሪው ናትናኤል ፈለቀ ትናንት ማክሰኞ መስከረም 24፣ 2009 ከስራ ሰዓት በኋላ ጸደቀ ድጋፌ እና አዲስአለም ሙሉጌታ ከተባሉ ሁለት የስራ ባልደረቦቹ ጋር በተለምዶ ‹ስታዲየም› ተብሎ የሚታወቀው አካባቢ በሚገኝው ‹ላሊበላ› ሬስቶራንት ውስጥ ተቀምጠው “ጮክ ብለው ‘የቢሾፍቱ ጭፍጨፋ የመንግስት ጥፋት ነው’፣ ‘እያሸበረ ያለው ራሱ መንግስት ነው’ በማለት አውረተዋል”፤ በሚል ምክንያት በፖሊስ ተይዞ ታሰረ፡፡ ናትናኤል እና ጓደኞቹ ዛሬ መስከረም 25፣ 2009 ጠዋት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቄራ ምድብ የወንጀል ችሎት ቀርበው የዋስትና ጉዳይ ለማየት አሻራ ይስጡና ነገ መስከረም 26፣ 2009 በድጋሚ እንዲቀርቡ ታዘው ወዳረፉበት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የካዛንችስና አካባቢው ፖሊስ ጣቢያ (በተለምዶ 6ተኛ እየተባለ የሚታወቀው) ተመልሰዋል፡፡

Natnael Feleke

ዞን ዘጠኝ አቋም

የናትናኤል እና የጓደኞቹ እስር አሁን አገሪቱ እየሔደችበት ያለውን መንገድ በሚገባ ያሳያል፡፡ ኢትዮጵያ ከጓደኞች ጋር ሰብሰብ ብለው የፖለቲካ ጉዳይ ማውራት የሚያሳስርባት አገር መሆኗም ለሁላችንም አሳዛኝ ነው፡፡ ስለዚህም ናትናኤልና ጓደኞቹ ሰውነታቸው ያስገኝላቸውን ሃሳባቸውን የመግለፅ መብታቸውን ከመጠቀማቸው ባለፈ ቅንጣት ታክል የሕግ መተላለፍ ያልፈፀሙ በመሆኑ አሁኑኑ ይፈቱ ዘንድ እንጠይቃለን፡፡

No comments:

Post a Comment