
ነሃሴ ላይ ከታሰረ በኋላ ጥቅምት ላይ በተደረገው አገር አቀፍ የሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ሽልማት ተሸላሚ በመሆኑ በጥቅምት ወር በተደረገው የሽልማት ስነስርአት እናቱ ወክለውት ሽልማቱን ተቀብለዋል ፡፡ ይህ በሽብር የተከሰሰ ወጣት አስተማሪ አይሲቲን በቀላሉ እና በሚገባ መልኩ ማስተማር የሚረዳ የፈጠራ ውጤት ባለቤት በመሆኑ ነው ሽልማት ያገኘው ፡፡ የሽልማቱ ቲሸርት እና ሜዳልያን ይዘው ሊጠይቁት የሄዱት እናቱ ሜዳልያውን ማስገባት ባይችሉም ቲሸርቱን አስገብተውለት ተመልሰዋል ፡፡ በማስተማር እና በፈጠራ ስራ የተሰማራው ይህ መምህር አንድም እውነተኛ ሽብተኛ ተከሶበት በማያውቀው ክስ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ዞን2 ይገኛል፡፡ በእርሱ የመምህርነት ደሞዝ ይተዳደሩ የነበሩ ቤተሰቦቹም እሱን ቅሊንጦ ድረስ እየሄዱ በመጠየቅ እየተንከራቱ ይገኛሉ ፡፡
ቢያንስ ኢንተርኔት ላይ ሼር በማድረግ የማናውቃቸው ብዙዎች ለሚከፍሉት ዋጋ እውቅናን እንስጥ
No comments:
Post a Comment