Tuesday, July 31, 2012

ፎንቱ ፎኒፍ ሪፈታ ጄናን ኢቲሌን ጂቢቻ ቲ ካቴ ("ስጋ ለስጋ ይደነግጣል ቢባል ጥጃ እንኳ በቁርበት ደነገጠች")


“አገሬ፣ አገራችን ኢትዮጵያ ነች። እንደ ኢትዮጵያዊ እንከራከራለን። ኢትዮጵያ መኖር አለባት። ሁላችንም የኢትዮጵያ አባል መኾን አለብን ብዬ ነው የማስበው።”

“የኢትዮጵያ አንድነት እና ነፃነት፣ እኩልነት ከተጠበቀ፣ በተፈጥሮ ሃብት የተደላደለች፣ በታሪኳ የገነነች፣ ኢትዮጵያ ሳትከፋፈል እና ሳትቆራረስ ለዘላለም እንድትኖር፣ የጎሳ ልዩነት ሳይደረግ በኢትዮጵያ ውስጥ የተወለደ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ኢትዮጵያዊነት ግዴታው እና መብቱም ነው ብዬ አምናለሁ፡፡”

 “I am so humbled and am forever grateful to our ancestors; no matter what mistakes they committed, they resisted all the colonizing powers in a way that made them create a history and logo that branded Ethiopia as the very idea of the decolonizing imagination.”

የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች [ኢ-መደበኛ] ቡድን አባል መሆኔ በዚህ ዓመት ከተከሰቱልኝ ምርጥ እውነታዎች ውስጥ በጣም ጠቃሚው ነው፡፡ ቡድናችን ‹‹የንባብ ፕሮግራም›› የተሰኘ በአንድ ርዕሰ ጉዳይ፣ አንድ ጽሑፍ ላይ ተመስርቶ በተወሰነ የጊዜ ዝላይ (Time Interval) መወያየት ጀምሯል፡፡

ይህ ጽሑፍ የዚህ ‹‹የንባብ ፕሮግራም›› ትሩፋት ነው፡፡ በእንዳልክ መራጭነት ‹‹Oromo Narratives›› የዶ/ር ዶናልድ ሌቪን ጥናት ላይ ለመወያየት ተጠራርተን ተገናኘን፡፡ ርዕሰ ጉዳዩ የኦሮሞ ብሔረሰብ የፖለቲካ ጥያቄዎችና አማራጭ መልሶች ላይ በጥቅሉ የሚያጠነጥን ነበር፡፡ በጉዳዩ ላይ የጠለቀ እውቀት ለሌለው ለእንደኔ ዓይነቱ ልብን በብርሃን የሚያጥለቀልቅ (enlights) የንባብና የውይይት ፕሮግራም ነበር፡፡ ይህንን ሳያካፍሉ መቅረት ስስት ነውና፣ ባይሆን እየቆነጠርኩ ላካፍላችሁ፡፡

Sunday, July 29, 2012

ፖካ ዮኬ፣ IDIOT PROOF; ETHIOPIA



በዚህ በምህንድስናው የትምህርት ዘርፍ ልብን የሚሰቅዝ ህሊናን የሚቆጣጠር ርዕስ ብዙውን ጊዜ አይኖርም፡፡በተለይ እንደኔ መሐል አዲስ አበባ በሚገኙ የድሆች መንደር ተወልዶ ያደገ ሰው ለራሱም ሆነ ለማኀበረሰቡ ችግሮች ከግል ጥረት እና ላቂያ በላይ መወቅራዊ መስተካከል እንደሚያሰፈልግ ሰለሚያምን ካልገባው ወይም ካልተሸወደ በስተቀር በሁለንተናው አይተጋም፡፡ምህንድስና ደግሞ ኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም “ተፈጥሮን በቁጥጥራችን ስር እናውላለን፡፡” ካሉት በተቃርኖ ተፈጥሮን ባለበት አኳኃን ከሳይንሳዊ ጥናቶች በመረዳት ለሰው ልጆች ጥቅም  የሚውልበትን መንገድ ማፈላለግ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በአጭር ጊዜ በስሎ የሚበላ ፣ ለብዙዎች ችጋር የወዲያው መፍትሔ የሚሰጥ አይደለም፡፡ የሚያጠግብ ቢኖር እንኳ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን የሚፈታ ሰው ሰው የሚሸት መፍትሔ አይሰጥም፡፡ብዙዎች ስሙን ከሩቅ ቢያከብሩትም ቆዳቸው ሳሳ ያለ ሰዎችን አይመስጥም፡፡አንዳንዴ ግን አልፎ አልፎ ልብን ላፍታ የሚያሸፍት ነገር አይጠፋም፡፡ዛሬ በምኞት መልክ እንድንጫወትበት ያሰብኩት ርዕስም ከነዚህ የአንድ ሰሞን የዐሳብ ግልቢያዎች በረከት የተገኘ  ነው፡፡

የአንድን ማሽነሪ ንደፍ የሚሰራ ሰው ከሚያደርጋቸው ጥንቃቄዎች ውስጥ አንዱ IDIOT PROOF ይሰኛል፡፡ይህም ማሽኑን የሚያመርተውን ፣ የሚገጥመውን፣ የሚያንቀሳቅሰው እና የሚጠግነውን ሰው ክህሎት እና ንቃት በመጠርጠር የሚጀምር ነው፡፡ ምንም እንኳን ሰውየው አስፈላጊው ዕውቀት ቢኖረው ፣ ተገቢውን ስልጠና ቢያገኝ እንኳ ይሳሳታል ተብሎ ይታመናል፡፡ይህም ከሰው ስህተት ከብረት ዝገት አይጠፋም እንደሚለው ሀገርኛ ቢሒል ያለ ነው፡፡ ከዚህ በመነሳት እንዲህ ያለ ስህተት ይከሰታል  ፤ እንዲህ አድርጎ ገልብጦ ይገጥመዋል ፤ የቀኙን ወደግራ የግራውን ወደቀኝ  ይቀያይረዋል ብሎ በመገመት ስህተት ፣ ሰህተቱን በመመንጠር የስራውን ክንውን ህጸጽ አልባ ማደረግ ነው ፡፡በኢቪየሽን እና ወታደራዊ ማሽኖች ላይ ስህተት ቢፈጠር ጉዳቱም የከፋ ስለሚሆን ይህ ደናቁርትን የማጥለል ጥበብ በብዛት ይስተዋላል፡፡  ማረፊያ ጎማው (landing gear) ተገልብጦ በተገጠመለት  አውሮፕላን ቢሳፈሩ ምን እንደሚፈጠር አስቡት? አያድርስ! ነው ብለው ፈጣሪዎን ይጠሩታል ወይስ ለአእዋፍ እንኳ ያልተፈቀደውን ዘላለማዊ በረራን ይመኙለታል? ጉድና ጅራት ከወደኋላ መሆኑን የተረዱት ፈረንጆቹ ግን በአጋጣሚ ይህን ማረፊያ ጎማ የሚገጥም ሰው  ከደናቁርት ወገን ሊሆን ስለሚችል ተስሳቶ እንኳን ገልብጦ እንዳይገጠመው አድርገው ከወዲሁ ያበጁታል፡፡ ጃፓኖች ይህንን ጥበብ ፖካ ዮኬ ይሉታል፡፡ትርጓሜውም  መወድቂያህን አሳምር ወይም በጥንቃቄ ውደቅ (fail-safing) እንደማለት ነው፡፡ለነገሩ  የምህንድስናውን አነሳው እንጅ በሌሎች የትምህርት ዘርፎችም  ይህ ስልት እንደሚተገበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡እስኪ ቅጥ አምባሩ ለጠፋው ቦለቲካችን ለምን  አንሞክረውም?

ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ - ስምንት


(ከሐምሌ 16 እስከ ሐምሌ 22፤ 2004)

Capital ጋዜጣ ‹‹Counting 20›› በሚል ርዕስ ባስነበበው የሽፋን ገጽ ታሪክ ላይ አቡነ ጳውሎስ የጵጵስና ‹‹ስልጣን›› የያዙበትን 20ኛ ዓመት አከባበር ይተርካል፡፡ በዓሉ በሸራተን አዲስ ሆቴል ሲከበር የተለያዩ ሃይማኖት አባቶች፣ የቢዝነስ ሰዎች እና የፖለቲካ ሰዎች ተገኝተዋል - ከነርሱም ውስጥ ቴዎድሮስ አድሃኖም እና ኃ/ማርያም ደሳለኝ ይገኙበታል፡፡

** ** **

Fortune  ጋዜጣ “Fineline” በተሰኘው የሚስጥር አምዱ ላይ ሰማሁ ብሎ ካንሾካሾካቸው ምስጢሮቹ ውስጥ መለስ ጁላይ 20 አዲስ አበባ ስለመግባታቸው፣ በርሳቸው ስም ተፈርመው የወጡ ዶክመንቶች ስለመኖራቸው እና እረፍታቸው ለአንድ ሳምንት ያህል የሚቀጥል መሆኑን ተናግሯል፡፡

** ** **

አዲስጉዳይ መጽሔት ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ ከፖለቲካ ሳይንስና የታሪክ ምሁሩ ፕሮፌሰር ገብሩ ታረቀ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ ይዞ ወጥቷል፡፡ ከቃለምልልሱ ውስጥ የተቀነጨበውን እነሆ፡-

Thursday, July 26, 2012

ባልቻን ፍለጋ

የመድፍ አረር አካባቢውን አጥኖታል፣ ጎራዴ ይብለጨለጫል፣ የደም ወንዝ ይጎርፋል፡፡ አዎ ይህ ጥቁር ጦር ቀላል  እንዳልሆነ እየታየ ነው፡፡ ያ የበጋ ሰማይ ደምን አየ መሰለኝ ክፉኛ ቀልቷል፡፡ በቀላ ሰማይ ስር ጦርን እንደ ብዕር ደምን እንደ ቀለም አድርገው ጀግኖች ታሪክ ይፅፋሉ፡፡ ታሪክን በመክተቡ መሀል ለጥቁሮቹ ጀግኖች አንድ አስደንጋጭ ነገር አጋጠማቸው፡፡ ከመሪዎቻቸው ንዱ የሆኑት ከጠዋቱ 3 ሰዓት ገደማ  ፊትአውራሪ ገበየሁ ተሰው፡፡ ወላድ በድባብ ትሂድ ገበየሁን ያጣ ጦር አልተበተነም ባልቻን የሚያክል መሪ አግኝቷልና፡፡ ደጃዝማች ባልቻም መድፉን እንደ ቀላል ያገላብጠው ጀመር፡፡ ይሄን የታዘበ አዝማሪም፡

 <<ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ፣
መድፍ አገላባጭ፣ ብቻ ለብቻ፡፡>>
ብሎ ተቀ፡፡ ምስጋና ለባልቻ፣ ምስጋና ለገበየሁ ያ ጥቁር ጦር ጠላቱን ድል ነሳ፣ አዲስ ታሪክም ፃፈ፡፡ የካቲት 23/1888 ዓ.ም አድዋ ኢትዮጵያ፡፡

ዛሬ ገበየሁ
አዎ እነ ገበየሁ እነ ባልቻ ታሪክ ከጻፉ ድፍን አንድ ምእተ ዓመት ሊሞላቸው 5 ዓመታት ብቻ ነው የቀረው ወቅቱም 1983 ዓ.ም ውልደቱ በታሪካዊዋ አድዋ የሆነ፣ ራሰ በሀ፣ ቀጭን-አጭር መሪ ነገሰ ኢትዮጵያን ሊያስተዳድር፡፡ የቀድሞው ፕሬዘደንት ያሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፡፡ መለስ እንደ ገበየሁ ከፊት ሆነው ህዝቡን ወደ ድል  ወይስ ወደ ገደል መሩት? ከተለያዩ አቅጣጫዎች የተለያዩ መልሶች ናቸው የሚሰጡት፡፡

Wednesday, July 25, 2012

ባርነት በዘመን ሲዋጅ?


ፍቃዱ አንዳርጌ
በሰባተኛው ክፍለ ዘመን ኋላ ቀሩ የአፍሪካ የባርነት ስርዓት በሁለት አፍሪካዊ ባልሆኑ ነገዶች እንደተጀመረ በጉዳዩ ዙሪያ የተፃፉ ፅሁፎች ያስረዳሉ፡፡ እነዚህ ሁለት የአረብ ሙስሊም እና የአውሮፓ ባሪያ አቅኝዎች በአፍሪካ ዙሪያ አሰፍስፈው በአፍሪካውያን ሰብዓዊነት ላይ ትልቅ ኪሳራ ሲያሳድሩ ከቆዩ በኋላም የአረብ ሙስሊም የባሪያ አቅኝዎች ከመመካከለኛው፣ከምዕራብና ከምስራቅ አፍሪካ የቃረሟቸውን ሰብዓዊ ፍጡሮች እስከ 20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ወደ ሰሜን አሜሪካና ኤዥያ በመላክ የሰው ላብ የገቢ ምንጫቸውን በማሳደግ ሃያልነታቸውን ለማስጠበቅ ሲታትሩ ቆይተዋል፡፡ አውሮፓውያኑም ቢሆኑ ከ15ኛው እሰከ 19ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ከምዕራብ፣መካከለኛውና ምስራቅ አፍሪካ በርካሽ የገዟቸውን አፍሪካዊ በትርፍ ወደ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣መካከለኛውና ደቡብ አሜሪካ በመሸጥ የሰብዓዊነትን ልዕልና ተጋፍተዋል፡፡እነዚህ በባርነት ስም ከተለያዩ የአፍሪካ ሃገሮች የሚጋዙት ምስኪኖች ትንሽ ከሚባል ስራ ጀምሮ እስከ ከባድ የጉልበት ስራ፣ ለጦርነት ፍጆታ ሲያገለግሉ ዘመናትን አሳልፈዋል፡፡

“የምክንያት ዘመን” እየተባለ የሚጠራው ሰብዓዊነትንና ምክንያትን ያማከለው ዘመን እያቆጠቆጠ በመጣበትና ከጨለማ ወደ ብርሃን ጉዞ በሚደረግበት ዘመን (age of enlightenment) እንዲሁም የኢኮኖሚው ስርዓት ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪው መሸጋገር ተከትሎ በምእራብ አውሮፓ የባሪያ ንግድ አብሮ እያከተመ ታሪክ ወደ መሆን ተቃረበ፡፡ በዚህን ጊዜ የምዕራቡ ዓለም የባሪያ ስርዓት ገበያው እንደ ጦፈ ነበር፡፡ የማታ ማታ ግን ብሪቴን በ1833 በሁሉም ግዛቶቿ የባርያ ስርዓትን ቀሪ ስታደርግ፣ ፈረሳይ በ1848 ቅኝ ለመግዛት በሰለጠነችባው ሃገሮች የስርዓቱን ቀሪነት በህግ ደንግጋለች፤ የተባበሩት አሜረካም ብትሆን በ13ኛው የህገ መንግስት ማሻሻያ አውግዛ ሰብዓዊነት እንዲልቅ አድርጋለች፡፡ ይህንን ተከትሎም በ1888 የአትላንቲክ የባሪያ ንግድ ላይመለስ ጦሱን ይዞ ቀርቷል፡፡ ቢሆንም ግን ይህ ባርነት ህገ ወጥ በሆነ መልኩ እሰከ 1930 ድረስ ሙሉ በሙሉ ሳይጠፋ ሰብዓዊነትን ሲጋፋ እንደቆዬ እሙን ነው፡፡

ይህ የባርነት ዘመን በአፍሪካውያን ላይ ታላቅ የሆነ የስነ ልቦና ኪሳራ ያሳደረ ከማሰብ መብት ጀምሮ እስከ መዘዋወር መብትን የነፈገ፣ የማንነት ቀውስጥ ውስጥ የጣለ፣ የበታችነት ስሜት እንዲዳብር ያደረገ፣ በተፈጥሮ የተሰጠውን ሰብዓዊ መብት የነፈገ “ዘመነ ንፉግ” ሆኖ አልፏል፡፡

ማን ስልጣን ላይ ተወለደና?

በናትናኤል ፈለቀ



Murder at 1600 ዊስሊ ስናይፕስ (Wisely Snipes) የተሰኘ ጥቁር አሜሪካዊ የሚተውንበት ልብ አንጠልጣይ ፊልም መጠሪያ ነው - Murder at 1600፡፡ 1600 (Sixteen hundred) የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች መኖሪያ የሆነው ዋይት ሀውስን በር ይዞ የሚያልፈው መንገድ መጠሪያ ነው፡፡

ፊልሙ የሚያጠነጥነው ስናይፕስ ዋይት ሀውስ ውስጥ ተገድላ የተገኘች ሴትን ነፍሰ ገዳይ እና የአማሟት ሁኔታ ለማጣራት በሚያደርገው ውጣ ውረድ ላይ ነው፡፡ ነፍሰ ገዳዩን ለማግኘት ስናይፕስ በሚያደርገው ክትትል በግድያው የፕሬዝዳንቱ እጅ እንዳለበት የሚጠቁሙ የጥርጣሬ መረጃዎች ያገኛል፤ ይህ ያልተዋጠላቸው የፕሬዝዳንቱ ቺፍ ኦፍ ስታፍ ስናይፕስን ደውለው ያስጠሩትና የዋሽንግተንን ማስታወሻ ሃውልት አሻግሮ የሚያሳየው ፓርክ ውስጥ የጠዋት ስፖርት እየሰሩ ስናይፕስን የክትትሉን ትኩረት ወደ ሌላ ተጠርጣሪዎች እንዲያዞር ወይንም ከነጭራሹ ቢተወው እንደሚሻል ለማስረዳት ይሞክራሉ፡፡ ስናይፕስ ግን የሚመለስ አልሆነም፤ እንደውም መረጃዎች የጠቆሙት ሰው እና ስልጣን ድረስ እንደሚሄድ አስረግጦ ይነግራቸዋል፡፡ ይህን ጊዜ ቺፉ ቆጣ ብለው ‹‹ፕሬዝዳንትነቱ ተቋም ነው (ግለሰብ አይደለም) እዛ እንድትደርስ አልፈቅድልህም›› ይሉታል፡፡

ስልጣን ተቋማዊ (Institutionalized) ሲሆን ምን ማለት ነው?

በታዳጊ ሀገራት ያሉ የመንግስት የአስፈፃሚ ቅርንጫፍ አናት ላይ የሚገኙ ባለስልጣናት ብዙ ጊዜ ሲፈፅሙ/ሊፈፅሙ ሲሞክሩ ከምናያቸው የፖለቲካ ቅሌቶች መካከል ስልጣን ላይ ለተጨማሪ ዓመታት ለመቆየት ሕገመንግስቱን ማሻሻል (ሴኔጋል እና ቬንዙዌላ የቅርብ ምሳሌዎች ናቸው)፣ ምርጫ ማጭርበርበር (ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ዚንባቡዌ)፣ በምርጫ ቢሸነፉም ስልጣን አለቅም ማለት (ኮትዲቩዋር) ይገኙበታል፡፡  እነዚህን የመሰሉ አሳፋሪ ድርጊቶች የሚፈፅሙት ታዲያ ስልጣንን የሚያዩት እንደህዝብን ማገልገያ መሳርያ ሳይሆን እስከ እለተ ሞታቸው የፈለጉትን እየፈለጡና እየቆረጡ የሚኖሩበት የግል ንብረታቸው አድርገው ስለሆነ ነው፡፡ ማቲያስ ባሰዶው እና አሌክሳንደር ስትሮህ የተባሉ የማህበራዊ ሳይንስ ጥናት ባለሙያዎች የፖለቲካፓርቲዎች ተቋማዊነት በታዳጊ ሀገራት በፈተሹበት ጥናት ተቋማዊነትን ሲተረጉሙ ‹ድርጅቶች እሴቶችን የሚመርጡበት እና ቀጣይነትን የሚያረጋግጡበት ሂደት ነው› ሲሉ ይገልፁታል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደማንኛውም ድርጅት ትውልድ ተሻጋሪነታቸውን ለማረጋገጥ ግልፅ የሆነ ስልጣንን (ቢያንስ ፓርቲ ውስጥ) ለተተኪዎች የሚያስተላልፉበት መመሪያ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ይህንንም ሽግግር የሚያበረታታ ስልጣን ህዝብን ማገልገያ መሳሪያ ብቻ እንደሆነ የሚያረጋግጥ የውስጠ ፓርቲ እሴት ያስፈልጋል፡፡ ኃላፊነትን ለመረከብ በጥሩ ሁኔታ የተኮተኮተ ተተኪ ማዘጋጀት እና ተተኪውም ብቁ መሆኑ ሲረጋገጥ ስልጣን (የፓርቲውንም ይሁን የሀገር) ማስረከብን አማራጭ የሌለው ምርጫ የሚያደርግ ባህል መፍጠርን ያካትታል ማለት ነው - ተቋማዊነት፡፡ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትን ማድረግ ያልቻለ እንደ ትልቅ ውድቀት የሚቆጠርበት በተለይም ስልጣን አልለቅም ብሎ ችክ ማለትን አሳፋሪ የሚያደርግ እሴት መፍጠር ወሳኝ ነው፡፡

Tuesday, July 24, 2012

ምናልባት፣ ምናልባት… ከመለስ በኋላስ?



የመንግስት ኮምንኬሽን ጉዳዮች በነገሩ ላይ አስተያየት ለመስጠት ቢሞክርም የአቶ መለስን “ቀላል ህመም” ከማመን ይልቅ አሁንም ኢትዮጵያ በዚሁ ዜና እውነትነት እና ውሸትነት ዙሪያ እየተናጠች ትገኛለች - የሚያሳምን እና የተረጋገጠ መረጃ የሚሰጥ እስካሁን አልተገኘም እንጂ! ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ታመዋል፣ ኧረ እንዲያውም ሞተዋል፣ አይ… መዳከም ነው እንጂ ደህና ናቸው… ወ.ዘ.ተ›› የሚሉ መላምቶች አሁንም በየፊናው ይሰነዘራሉ፡፡ ይህ ዜና እየተናፈሰ ባለበት በዚህ የውጥረት ሰሞን አንድ የመንግስት ኃላፊ ወጥቶ ትክክለኛ መረጃ ለመስጠት ረዥም ጊዜ መውሰዱ መንግስትን ትዝብት ላይ ቢጥለውም ከአቶ በረከት መግለጫ በኋላ ደግሞ የመረጃው ትክክለኛነት ለማመን እንኳን ሳይሞክሩ፣ ብዙዎች በተከታዩ የድኅረ መለስ ዘመን ላይ እያወሩ ይገኛሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ (እንደ ኮምንኬሽን ሚኒስትሩ ንግግር ቀላሉን ያርግላቸውና) ከዚህ በኋላ  አገሪቱን መምራት የማይችሉበት ሁኔታ ቢፈጠር ቀጥሎ ምን ይከሰት ይሆን?›› የሚለው ልብ አንጠልጣይ ጥያቄም በተለያዩ ሰዎች እና አካላት ዘንድ የመወያያ አጀንዳ እየሆነ ይገኛል፡፡

የአቶ መለስ አለመኖር…
የኅወሓት ‹‹የነፍስ አባት›› አቦይ ስብሃት ነጋ በቅርቡ ከቪኦኤ ጋር በነበራቸው ንግግር የአቶ መለስን በጊዜያዊነትም ሆነ በቋሚነት አለመኖር አቃለው ሃገሪቷ በአመራር ደረጃ የሚያጋጥማት ክፍተት እንደማይኖር ተናግረዋል፡፡ ይህ እንግዲህ ከአንድ የበታች አመራር ካድሬ የተሰጠ ሐሳብ ቢሆን ኖሮ ‹‹የፓርቲውን እና የመንግስትን አሠራር ያልተረዳ፣ የዋህ፣ ልማታዊ›› ብለን እናልፈው ነበር፡፡ ጉዳዩን የተናገሩት ግን የፓርቲው ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ እነደመሆናቸው መጠን የመለስ አለመኖርን ክፍተት ለመረዳት የመረጃ እጥረት አለባቸው ተብሎ አይታሰብም፡፡ በሌላ በኩል ክፍተቱ ቢኖርም እንኳን፣ አቦይ ስብሓት ክፍተት አለ ብለው እንዲሉ መጠበቅ የዋህነት ነው፡፡
 
የአቶ መለስ ስልጣን ለረዥም ዓመታት ተለጥጦ መቆየቱም ብዙም የሚያወያይ እና የሚያከራክር አይደለም፡፡ በተለይ በተለይ በአሁኑ ወቅት በዋናነት የሚታዩትን የመንግስት ዋና ዋና ዕቅዶች (የእድገት እና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን እና የግድብ ግንባታውን ጨምሮ) አርቃቂ እና ባለቤት እንደሆኑ ይነገራል፡፡ የዚህ “ከአቅም በላይ የተንጠራራ” ዕቅድ አፈጻጸምን ያለሳቸው ማሰብ ትንሸ አስቸጋሪ ይመስላል፡፡ በተለያዩ ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች አሠራር እና አፈጻጸም ላይ ጠንካራ እጃቸው በተደጋጋሚ ይገባል፣ ለውሳኔም ይቃጣሉ ተብለው የሚታሙት አቶ መለስ ከቤሮክራሲው መጥፋታቸው የሚታይ ክፍተት መፍጠሩም የማይቀር ነው፡፡ ለኢኮኖሚያዊ ትንታኔው፣ለመንግስት ስህተቶች መከላከሉ፣ ለልማትና ጥፋቱ ማብራሪያ ባለፉት አሥር ዓመታት በብቸኝነት ብቅ የሚሉት መለስ አለመኖራቸው፣ “የፋጡማን አለመኖር” ያህል ነው ብሎ በቀላሉ ማለፍ ለማንም የፖለቲካ ንቃት ላለው ኢትዮጵያዊ የሚዋጥ አይመስልም፡፡ ሌላው ቀርቶ በሕጋዊው የፍትህ ስርዓት የማይፈቱ የሚመስሉ ጉዳዮችን የመጨረሻ እልባት የመስጠት ድረስ ስልጣን ያላቸው አቶ መለስ መሆናቸው እየታወቀ ይህ ለዓመታት የተገነባን “ሁሉ ያገባኛል”  ስብዕና አለመኖር የሚፈጥረው ክፍተት የሚካድ አይደለም፡፡

Monday, July 23, 2012

መለስ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን



ኢትዮጵያ ድፍን የ25 ብር ኖት የላትም፤ ሆኖም ሊዘጋጅላት ነው ብለን እናስብ:: በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ ናቸው ተብለው የሚታመንባቸው መሪዎች ምስላቸው በዚህ የብር ኖት ላይ ታትሞ እንዲወጣ ቢፈለግ፣ ኢትዮጵያውያንን የሚያስማሙ መሪዎች አሉን? አቶ መለስስ ለዚህ ማዕረግ በስንቱ ኢትዮጵያዊ ይታጩ ይሆን? ብለን ብንጠይቅ:: መልሱ አዳጋች ነው:: እንደበለፀጉት ሀገሮች ነጻ የሆነ የሕዝብ አስተያየት የሚሰበስብ የሚዲያም ሆነ የህዝብ ግንኙነት ድርጅት በሌለበት እንደ ኢትዮጵያ ባለ ሀገር አቶ መለስን አብዛኛው ሕዝብ ‹ይወዳቸዋል› ወይም ‹ይጠላቸዋል› ብሎ አፍን ሞልቶ መናገር ይከብዳል:: እንደ አፄ ምንሊክ ወይም እንደ አፄ ኃይለስላሴ የኢትዮጵያዊያንን አስተያየት በተለያየ መስመር እንደማይበታትኑ መናገር ግን አይከብድም:: ከሕዝብ ዕይታ ከተሰወሩ ወዲህ እንኳን፣ ስለጠቅላይ ሚንስትሩ በየማህበራዊ ድረገጾች እና በየጦማሮቹ የሚጻፉት ጽሁፎች የተቃውሞ እና የድጋፍ በማለት ለሁለት መክፈል ይቻላል:: ለመሆኑ አቶ መለስ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን እንዴት ይታያሉ?
ባልደራባዬ አቤል ጠቅላያችን የማን ናቸው? ብሎ በጠየቀበት ጦማሩ ‹‹ኢትዮጵያውያን እርሳቸውን የኔ ብለው ለመቀበል ይቸገራሉ፤ በግድ አስገድደው ያንተ ነኝ ካላሉት በቀር ሁሉም እርሳቸውን መሪዬ ናቸው ብሎ ለመቀበል አይፈልግም›› ይለናል:: ነገር ግን ባለፉት ሃያ አንድ ዓመታት የኢሕአዲግ የፊት ገጽ ሆነው የቆዩት አቶ መለስን ኢትዮጵያውያን እንዴት ያዩዋቸዋል የሚለውን ለመረዳት የኢሕአዲግን የአስተዳደር ስረዓት በቅጡ መረዳት ያስፈልጋል::

ኢሕአዲግ በቁመናው ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ድርጅት ቢመስልም ሊቀመንበሩ አቶ መለስ ዜናዊ በጠና ታመዋል የሚል ወሬ ሲናፈስ በፓርቲው አባላት መንደር የሚስተዋለው አለመረጋጋት ብሎም የሚወራው የስልጣን ሽኩቻ የኢሕአዴግን ሀገር አቀፍነት ሳይሆን በአቶ መለስ ዜናዊ ሙሉ ቁጥጥር ስር የወደቀ ፓርቲ መሆኑን የተለያዩ ተንታኞች ይናገራሉ:: አቶ መለስ እና ደጋፊዎቻቸው ኢትዮጵያን በአዲስ መንገድ ለመስራት መንገድ ጀምረናል ብለው ቢናገሩም ከተቀናቃኞቻቸው እና ተቃዋሚዎቻቸው ግን ቀድሞ ከነበሩት የኢትዮጵያውያን የአገዛዝ ስርዓቶች ምንም የተለያ ነገር እንዳላመጡ ይባሱንም ሀገሪቱ የነበራትን መልካም እሴቶች እንዲሸረሸሩ ምክንያት ሆነዋል ብለው ይወቅሷቸዋል::

Sunday, July 22, 2012

ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ - ሰባት


(ከሐምሌ 9፣ 2004 እስከ ሐምሌ 15፣ 2004)

ሪፖርተር  በረቡዕ ዕትሙ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ በመልካም ጤንነት ላይ መሆናቸው ተሰማ›› የሚል ዜና አስነብቦናል፡፡ ‹‹በ21 ዓመታት የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በጤንነት ችግር በ19ኛው የአፍሪካ መሪዎች ስብሰባ ላይ ያልተሳተፉት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመልካም ጤንነት ላይ መሆናቸው ተሰማ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ የውጭ ሕክምና ክትትላቸውን ጨርሰው ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱም ምንጮች ገልጸዋል፡፡ …››

** ** **
‹‹የሚኒስትር ጁነዲን ሳዶ ባለቤት ከሳዑዲ ዓረቢያ የሃይማኖት አታሼ ቢሮ ገንዘብ ይዘው ሲወጡ ተያዙ›› የሚል ዜና ያስነበበን ሰንደቅ ጋዜጣ ነበር፡፡ ‹‹…[ወ/ሮ ሃቢባ ሐምሌ 10፣ 2004] …ግምቱ ከሃምሳ ሺ እስከ መቶ ሺ ብር የሚገመት የታሰረ ገንዘብ እና በዓረብኛ የተጻፉ መጽሐፍት ይዘው ሲወጡ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን ምንጮቻችን ገለጹ፡፡…››

** ** **

ፍትህ ጋዜጣ ከጋዜጦች ሁሉ ተለይቶ በዚህ ሳምንት አልወጣም፡፡ የጋዜጣው ከፍተኛ አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ በፌስቡክ ገጹ ችግሩ ከአሳታሚው አለመሆኑን እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ ‹‹ዛሬ አርብ ነው፤ ፍትህ ግን አንባቢያን ጋር አልደረሰችም፡፡ በእርግጥ ትላንት የጋዜጣው የሽያጭ ሰራተኛ ብርሃና ሰላም ማተሚያ ቤት ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ተገኝቶ ለ30 ሺህ ኮፒ 80385 (ሰማኒያ ሺህ ሶስት መቶ ሰማኒያ አምስት) ብር ከፍሏል፡፡ የፍትህ ህትመት ክትትልም እኩለ ሌሊት ላይ ማተሚያ ቤት ቢደርስም የህትመት ክፍል ሀላፊው ‹‹ፍትህን እንዳታትሙ ተብለናል›› በሚል ጋዜጣዋ ሳትታተም አደረች፡፡

Saturday, July 21, 2012

የመለስ ዜናዊ ፲ ታላላቅ የአፍ ወለምታዎች


የዞን ዘጠኝ ነዋሪዎች የሆኑት በፈቃዱ ዘ ኃይሉ የመለስ ዜናዊ ‘ሀሁ’ በስልጣን ጎዳና እንዲሁም ዘላለም ክብረት መለስ ወደ ውጭ - መለስ ከውጭ በሚል ርዕስ ሁለት ጦማሮች አስነብበውናል፡፡ ይህም ስለጠቅላያችን የጤና ሁኔታ ከነበረው ውዝግብ መለስ ብለን ሌሎች ሁኔታዎች እንድንቃኝ ዕድል ሰጥቶናል ፡፡ዛሬ ቀኑ ቅዳሜ ነው፤ እሰኪትንሽ ቅዳሜ ቅዳሜ የሚሸት ነገር እያወራን ዘና እንበል በሚል ደግሞ ይችን ጽሑፍ ከዱራሜ ዶት ኮም ያገኘነውን የጠቅላያችንን አስር ታላላቅ የአፍ ወለምታዎች ፣ በዚህ ንግግራቸው የተገረመው አብዛኛው ሰው ወደሚሰማው ቋንቋ እንደወረደ ተርጉመን ለአደባባይ አውለነዋል፡፡


፲. በ1983  ዓ.ም. በለንደኑ ጉባዔ  በኢህአዴግ ታርጋ የተሰባሰቡት ቡድኖች የፓርቲያቸው ህወሓት ተቀጥላ እንደሚሆኑ ለአሜሪካና ብሪታኒያ ባለስልጣናት አረዷቸው፡፡ብሪታኒያውያኑ ይህንን በተቃወሙ ጊዜ ቁጣቸው በግልጽ የሚታየው አቶ መለስ እንዲህ አሉ፡፡

     “አንድ ነገር ግልጽ ላድርግ  ፤ ከጉባዔው በኋላ  ኢህአዴግ የሚባል መንግስት አይኖረንም፡፡”

           
፱.  በ1985/6  ዓ.ም. ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ ያላቸውን እይታ በአንድ ቃለ መጠይቅ ማብቂያ ላይ እንዲያካፍሉ ከአንድ ዘጋቢ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ መለስ እንዲህ ሲሉ መለሱ፡፡

     “የኢትዮጵያ ዕድሜ መቶ አመት ብቻ ነው ፤ከዚህ በቀር ሌላ  የሚያወሩት ራሳቸውን በተረት ተረት እያሞኙ ነው፡፡" 

Friday, July 20, 2012

መለስ ወደ ውጭ - መለስ ከውጭ


መጋቢት 25/1982 ዓ.ም ዋሽንግተን ዲሲ 14ኛው መንገድ ቦታውም የህወሀት ፅ/ቤት፡፡ አንድ ያለማቆም ሲጋራ የሚያጨሱ በፅ/ቤቱ በባዶ እግራቸው ዘና ብለው ቁጭ ያሉ፣ እንግሊዘኛቸው የሚያምር በኢትዮጵያዊ የንግግር ዘይቤ የተካኑ ወጣ  ከቀድሞው የCIA ኤጀንት እንዲሁም አፋቃሬ ኢትዮጵያዊው (Ethiopianist) ፖል ሄንዝ ጋር ለውይይት ቁጭ ብለዋል፡፡ በንግግራቸው መጀመሪያም ወጣ ፖል ሄንዝን እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፡

‹‹አንተ የፃፍካቸውን ብዙ ነገሮች አንብቢያለሁ በሁሉም ነገሮችህ እስማማለሁ ነገር ግን ለምን ማራክሲስቶች እያልክ ትጠራናለህ?››

ፖል ሄንዝም፡ 
 ‹‹ምክንያቱም እናንተ እራሳችሁን ማርክሲስቶች ነን እያላችሁ ስለምትጠሩ ነው፡፡ አልባኒያን እንደ ሞዴል አድርገን የተቀበልን ነን ትላላችሁ፡፡ ለስታሊንም ተለየ ፍቅር እንዳላችሁ ሪፖርቶች ያሳያሉ‹‹ ይሏቸዋል፡፡

 ወጣ ቀበል አድርገው: ‹‹እኛ ማርክሲስት-ሌኒኒስት እንቅስቃሴዎች አይደለንም፣ በትግራይም ማርክሲዝም እና ሌኒኒዝምን ተግባራዊ አናደርግም፡፡ አዎ አንዳንድ አባላት ማርክሲስት ሌኒኒስት ሊሆኑ ይችላሉ እኔም በተማሪነት ዘመኔ ነበርኩ፣ አሁን ግን አለም ላይ ምን እየተካሄደ እንዳለ እናውቃለን፣ የውጭ ርዕዮተ አለምም ለኛ መፍትሄ ይሆናል ብለን አናምንም፣ የራሳችን ባህል እና ወግ የጠበቀ ስርዓት መፍትሄ ነው ብለን እናምናለን›› በማለት ተኮት ተው ያደጉበት ማርክሲዝም በካፒታሊዝሙ አለም መሪ ዋና ከተማ ቀበሩት::


የ ያኔው ወጣት  የዛሬው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ናቸው::

Wednesday, July 18, 2012

የመለስ ዜናዊ ‘ሀሁ’ በስልጣን ጎዳና


መለስ ዜናዊ (የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር)
ልደት፡- ሚያዝያ 30፣ 1947
የኅወሓት ሊቀመንበርነት፡- ከ1981 ጀምሮ
የኢሕአዲግ ሊቀመንበርነት፡- ከ1981 ጀምሮ
የኢትዮጵያ ፕሬዚደንት፡- ከ1983 – 1987
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር - ከ1987 - አሁን
“ብልቡ ዝሸፈተ ምመልሲ ይብለን” ይባላል በትግርኛ፤ ‘በልቡ የሸፈተን የሚመልሰው የለም’ እንደማለት!

የታሪኩ መጀመሪያ

የሕወኅት ወላጅ ከሆነው ማገብት (ማኅበር ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ) መስራች አባላት አንዱ የሆኑት አረጋዊ በርኸ (ከነፃ አውጪ ታጋይነት ወደምሁርነት የተሸጋገሩ ስደተኛ ምሁር ናቸው፤) The Origin of The Trigray People’s Liberation Front በሚለው ጥናታቸው ላይ እንዳሰፈሩት መጀመሪያ ትግራዋይ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ሕብረት ተፈጠረ፡፡ የኅብረቱ አባላት ከሆኑት ውስጥ መለስ ተክሌ እና አባይ ፀሃዬ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ማሕበሩ አርታኢ ቡድንን ይመሩ ነበር፡፡ የኅብረቱ ዋነኛ ዓላማ ለትግራይ ሕዝቦች ፖለቲካዊ ንቃት ማጎናፀፍ ብቻ ስለነበር፣ ከዚያ የተሻለ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንዲችል በሚል ማገብት ተወለደ፡፡ ማገብት የኅወሓት ወላጅ እናት ነው፡፡

ማገብት ሕወሓትን ከመመስረቱ በፊት ከኅግሓኤ (ሕዝባዊ ግምባር ሓርነት ኤርትራ) ጋር የሥራ ግንኙነት መስርቶ ነበር፤ (ስሙም ከዚያው የተገኘ ይመስላል፡፡) መለስ ከኅወሓት፣ ጥቂት ቀደምት አባላት አንዱ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ መጽሐፍት እንደሚተርኩት መለስ ዜናዊ እና አቦይ ስብሓት የኅወሓት መስራች ሳይሆኑ፣ ከተመሰረተ ጥቂት ወራት በኋላ ትግሉን የተቀላቀሉ መሆናቸውን A Political History of the Tigray People’s Liberation Front (1975-1991): Revolt, Ideology and Mobilisation in Ethiopia በተሰኘው የዶክትሬት ድግሪ ማሟያ ጽሑፋቸው ላይ አረጋዊ በርኸ ጽፈዋል፡፡ 

Sunday, July 15, 2012

ነፃ ሐሳብ የማያውቁት ኤፍኤሞቻችን


ኤፍሬም ማሞ

1984 ዓ.ም በአገራችን የመገናኛ ብዙሃን ጨዋታ የተለወጠበት ነው፡፡ የደርግ መውደቀትን ተከትሎ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በፕሬስ ህጉ እውን ሆነ፡፡ የግል ጋዜጦችም እንደ አሸን ፈሉ፡፡ የፕሬስ ህጉ በታወጀበት የመጀመሪያ አምስት አመታት ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ የህትመት ውጤቶች ዕውን እንደነበሩ ይታወሳል፡፡ በአሁኑ ሰዐት ያሉትን መሰል የህትመት ውጤቶች መቁጠር እጅግ ቀላል ስራ መሆን አለበት፡፡

የ 1987ቱ ህገ መንግሰት ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብትን ቢደነግግም የማሰራጫ መገናኛ ብዙሃንን በተመለከተ ግን በፈቃጁ አካል እሽታን ለማግኘት እሰከ 1991 ዓ.ም መጠበቅ ነበረብን-የብሮድካስት ህጉ እስከሚወጣ ድረስ፡፡ ይህም ሆኖ የግል ሬዲዮና ቴሌቪዥን ነገር የውሃ ሽታ እንደሆነ ስምንት አመታት አለፉ፡፡ በ 1999 ዓ.ም ከአመታት ጥበቃ በኋላ 15 አመልካቾች ለነበሩበት ዘርፍ ለሁለቱ የግል ባለቤቶች የአየሩ ሞገድ ተፈቀደላቸው-ቁጥራቸው አፍሮ ኤፍ ኤምን ጨምሮ ከሶስት ከፍ ለማለት ግን አልቻለም፡፡ የቴሌቪዥኑ ነገር አሁንም እየታሰበበት ነው፡፡ 

የአፍሪካን መገናኛ ብዙሃን በጥልቀት በማጥናት ታዋቂ የነበሩት ዛምቢያዊው ፍራንሲስ ካሶማ የሬዲዮ እጅግ አስፈላጊነት ጎልቶ የሚወጣው በቀውስ ወቀት እንደሆነ  ይገልጻሉ፡፡ በርካታ የመፈንቀለ መንግስት ሙከራን ባሰተናገደችው አፍሪካ የሬዲዮ ጣቢያዎች የጦር አውድማ እንደሚሆኑና ጣቢያውን ያልተቆጣጠረ ቡድን ጥረቱ ሁለ ከንቱ እንደቀረ ጽፈዋል፡፡

የግል የህትመት ውጤቶች ገና ከመጀመሪያው በስልጣን ላይ ያለውን መንግስት ማጥላላት ስራዬ ብለው ያዙ የሚለው ሐሌሉያ ሉሌ በ1999 የጻፉት የሁለተኛ ዲግሪ ማሟያ ጽኁፍ ነው፡፡ ጸሃፊው ከነጻ ፕሬስ አዋጅ መውጣት በኋላ የወጡ በርካታ የህትመት ውጤቶች በከፍተኛ ደረጃ የብቃት ማነስና የጋዜጠኝነት ሙያ ስነምግባር እጥረት የነበረባቸው፤ እንዲሁም የተፈቀደውን ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ካለልክ መጠቀም ያበዙ ነበሩ ይላሉ፡፡ አክለውም እነዚህ አሳታሚዎች ገለልተኛ ሆነው አለመገኘታቸውና አለማቀፋዊ ተቀባይነት ያላቸውን የጋዜጠኝነት መርሆች ለመከተል አለመፈለጋቸውን እንደ ዋና ችግር ይጠቅሳሉ፡፡

ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ - ስድስት


(ከሐምሌ 2 እሰከ ሐምሌ 8፣ 2004 - Find the original at http://zone9ethio.blogspot.ca/)

ሰለሞን ስዩም ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ላይ ‹‹የኢሕአዴግ ጥንካሬ ምን ያክል ነው?›› የሚል ርዕስ በሰጠው ሐተታው፣ ‹‹…እንቁላል በሁለቱ ጫፍና ጫፍ (በዋልታዎቹ) በመዳፍህ መካከል አይሰበርም፤ በወገቡ በኩል በመዳፎችህ መካከል ከተጫንከው ግን ፍርክሽ ይላል፡፡…›› የሚል ቀላል መልስ ሰጥቷል፡፡

** ** **

ሪፖርተር ጋዜጣ በረቡዕ እትሙ ‹‹አቶ ጁነዲን ሳዶ ስለ ኮብል ስቶን ያደረጉት ንግግር ተቃውሞ ገጠመው ›› በሚል ርዕስ ባሰፈረው ዜና ላይ የሚከተለውን አካትቷል ‹‹የቀድሞው ድምቀቱና ውበቱ በተለየው የዘንድሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ሥነ ሥርዓት ላይ፣ የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትሩ አቶ ጁነዲን ሳዶ በንግግራቸው ስለ ኮብል ስቶን በማንሳታቸው ከፍተኛ የተቃውሞ ጩኸት ገጠማቸው፡፡ አቶ ጁነዲን ባለፈው ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ንግግራቸውን ሲጀምሩ በአድናቆት ጭብጨባና በፉጨት ቢታጀቡም፣ ድንገት የንግግራቸውን አቅጣጫ ወደ ኮብል ስቶን በማዞራቸው ነበር ሳይታሰብ ከፍተኛ የተቃውሞ ጩኸት፣ ጉርምርምታና ፉጨት ከተመራቂዎቹ የተሰማው፡፡…››

** ** **

ፍትህ ጋዜጣው ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ የፕሮፓጋንዳ ስምምነት አለን በሚል የአልሻባብ ሰው ነኝ ከሚል የተጻፈለት ኢሜይል ተከታይ አሁንም በሌላ ሰው ተላከለት፡፡

Saturday, July 14, 2012

ጠቅላያችን የማን ናቸው?

 
ሰሞኑን የጠቅላያችን ጤና በጽኑዕ መቃወስ የሚያወሱ ጭምጭምታዎች ከተለያየ አቅጣጫ እየተናፈሱ ይገኛሉ፡፡አንዳንዶቹ እንደውም ስለ ድህረ መለስ ኢትዮጵያ እና ስለተተኪዎች የምር መነጋገር ይዘዋል፡፡እንደው አያድርገውና! ድንገት ጸጥ ቢሉ መቃብራቸው ላይ የሚነበብ አጭር የህይወት ታሪካቸውን የመጻፍ ሃላፊነት  ቢሰጠን ምን እናደርግ ይሆን? አንድ የኔ ብጤ ተርታ ሰው ቢሆን ብዙም አያስቸግርም፡፡ የእርሳቸው ለመጻፍ   ግን  የህይወት ታሪክ  እና  ሌላውን መደበኛ ታሪክ (history and biography) ማጣቀስ ተገቢ ነው:: ለዚህ ደግሞ ሁነኛው የትምህርት ዘርፍ የስነ ማኅበረሰብ ጥናት (sociology ) ነው፡፡

እንደ የስነ ማኅበረሰብ ጥናት ባለሙያዎች  ትንታኔ ሰው በዕለት ተዕለት ጉዳዮቹ ወስጥ የተለያዩ ማኀበራዊ ማነቆዎች ያጋጥሙታል፡፡አንድ ማእከላዊ ሰው (average person) እነዚህ ያገጠሙትን እክሎች(traps)  አልፎ የግሉን ችግሮች ከትልቁ ስዕል (ከሚኖርበት ማኀበረሰብ ፣ ከዓለም ታሪክ) ጋር ለማያያዝ ይከብደዋል፡፡ ከዚህ ይልቅ ከራሱ ትንሽ ዓለም (መንደር ፣ ጎሳ ፣ ት/ቤት ፣ መ/ቤት) አንጻር  መረዳት ይቀናዋል፡፡ ጥቂቶች ነገር ግን የመንፈስ ልዕልና (quality of mind)  ያላቸው ግላዊ ጉዳዮችን ከማኅበረሰብ ጋር አጣምሮ ለማየት የሚያስችል ማኀበረሰባዊ ነጽሮት (Sociological imagination) አላቸው፡፡

ስነ ማኅበረሰባዊ ነጽሮት  ብዙ ፍሬዎች አሉት፡፡ የራስን የህይወት ልምድ ከታሪክ አጋጣሚና ከማኅበረሰባዊ መዋቅሮች ጋር በማገናኘት እድል ፈንታ ጽዋ ተርታን ለመለካት ይጠቅማል፡፡ እንዲሁም  በማኅበረሰብ ውስጥ የራስን ሚና መለየትና ራስን ለአንድ ስፍራ ለማጨት ያስችላል፡፡  በዚህ ዘርፈ ብዙ ማኀበረሰብ ውስጥ የኔ ስፍራ  የት ነው?  የሚለውንም  ጥያቄ ለመመለስ የሚደረግም ሐሰሳ ነው፡፡ በዚህ ነጽሮት ተጠቅመው የራሳቸውን፣ የቤተሰባቸውን፣ የመንደራቸውን ችግር የፈቱ ሰዎች ‘የራሳቸው ናቸው’ ለማለት ይከብዳል፡፡ ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ የፈጠሩት ደግሞ የሁሉ ሰው (global citizen or cosmopolitan person) ተብለው ይጠራሉ፡፡ በእኛም  ማኅበረሰብ ውስጥ እንደዚህ ህዝበ አዳም የኔ የሚላቸው አልፎ አልፎ ይታያሉ፡፡ በየእደሩ፣ በዕቁብና በጽዋ ማኅበራት ከማዕከላዊነት አልፈው ከቤተሰባቸው በላይ ለአከባቢያቸው ማኅበረሰብ የሚተጉ ሰዎች አልጠፉም፡፡ እንደዛሬ የመቅለል ዘመን ሳይመጣ፣  የረባ ሚኒስቴር ሳይጠፋ በፊት   በዓለም አቀፍ ተቋማት በማገልገልም የዓለምን ህዝብ የጠቀሙ ጠንካራ ዲፕሎማቶችም  ነበሩን፡፡ እንግዲህ ይህን መሰረት አድርገን ነው የጠቅላያችንን አጭር የህይወት ታሪክ ለመጻፍ ጥረት የምናደርገው፡፡ በነጽሮታቸው መጠን ለማኅበረሰባቸው ባበረከቱት አስተዋጽኦና ይህን ተከትሎ ከማኅበረሰቡ የሚሰጥ  “የኔ ነህ  ፣ጀግናዬ  ነህ፣” ከሚል ማዕረግ፡፡ በአንድ ቃለ መጠይቅ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ስለጠቅላያችን ጭንቅላት ምጥቀት ሲናገሩ “ገንዘብ ለማግኘት ብፈልግ እርሱን ከዚህ አስወጥቼ  ሌላ ስራ እንዲሰራ ነው የማደርገው” ማለታቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡ ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ እንዳይሆንብን እርሱን ትተን በርዕሰ መንግስትነት ለሁለት አሥርት ዓመታት ካስተዳደሯት ኢትዮጵያ ተነስተን ‘የኢትዮጵያ ናቸው/ አይደሉም ?’ ብለን እንጠይቃለን፡፡

Thursday, July 12, 2012

ስለምንስ ከምሁራን መካከል ትፈልጉኛላችሁ? !

የትምህርት ጉዞው የተጠናቀቀ ይመስላል፡፡ ተማሪዎች በምረቃ ቀን የሚለብሱት ጋወን ፣ አስመራቂ ቤተሰቦቻቸው ወደ ምረቃው ቦታ የሚገቡበት የመግቢያ ትኬት ከየትምህርት ክፍላቸው እየወሰዱ ነው፡፡ አንድ ከዚህ በፊት ያልተለመደ ተግባር ግን ይቀራል፡፡ የአንድ ሙሉ ቀን ስልጠና፡፡ ከጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማት በመጡ ባለሙያዎች ከምረቃ በኋላ ሊሰማሩባቸው ስለሚችሉባቸው የስራ አይነቶች፡፡

ገነትም ከነዚህ ሰልጣኞች መካከል አንዷ ስትሆን በ3 አመት የዩንቨርስቲ ቆይታዋ Applied Biology ያጠናች ስትሆን ከተቻለ አንድ ፋርማሲ ሰራተኛ ውስጥ አለዚም መምህር እሆናለው የሚል ህልም ነበራት፡፡ በስልጠናው የሰማችው የስራ መስክ ግን አልተዋጠላትም፡፡ ተደራጅቶ የባልትና ውጤቶችን መሸጥ፣ የከተማ ግብርና ላይ መሰማራት፣ የኮብል ስቶን ማንጠፍ ስራ፣ፓርኪንግ ወ.ዘ.ተ፡፡

ይህ በ2004 ዓ.ም ተማሪዎቻቸውን ያስመረቁ የሁሉም የመንግስት ዩንቨርስቲዎች እና ተማሪዎች ሰሞነኛ ቆይታ ነው፡፡

ትምህርት

የሰው ልጅ ሁሉን ያውቅ ዘንድ አይቻለውም ስለዚህም ስለ ክዋክብቱ መረዳቱ የበዛለት ላላወቀው እሱም ስለ ስነ ተዋልዶ እውቀቱ ከሌለው ከአዋቂው የሚቀስምበት ስርዓት ነው ትምህርት፡፡ አንድ ሰው አቃቂ ምሁር ይባል ዘንድ በሁሉም የትምህርት ዘርፎች የዕውቀት ላቂያ ይኑረው ያኔም አዋቂ ይባላል ይለናል የRenaissance Man Theory፡፡ ለዛም ይመስላል በአብርሆት ዘመን (15-18 Century) የነበሩ ምሁራን ሁሉን አቀፍ እውቀት ነበራቸው ልንል የምንችለው፡፡ የፍልስፍና፣ የሂሳብ፣ የስነ-ክዋክብት፣ የስነ-ሰብ ወ.ዘ.ተ እውቀቶችን አንድ ምሁር አቅፎ ሊይዝ ይችል ነበር፡፡

ይሄ ትክክል አይደለም ይልቅስ በህብረተሰቡ ውስጥ እምርታ ይመጣ ዘንድ የስራ ክፍፍል (Division of Labor) ወሳኝ ነው ብሎ ስኮትላንዳዊው የስነ-ምጣኔ ምሁር አዳም ስሚዝ የሀሳብ ሽግግር ካደረገ ወዲህ፡፡ እያንዳንዱ ህብረተሰቡ አካል አንድ የስራ መስክ ላይ በተለየ(Specialize) አድርጎ ጥናት ካደረገ እና ከተማረ በዘርፉ ትልቅ አስተዋፅኦ ያመጣል በሚል የትምህርት ስርዓቶቹም በዚህ ሀሳብ መቀረፅ ጀመሩ፡፡ ባጫ ምህንድስና ፣ አበበ ህግ ፣ አይዳ እርሻ ወ.ዘ.ተ እየተማሩ በያዙት ሙያ ላቂያን ማሳት ይችላሉ የሚለው የ Specialization Theory አሁን ድረስ በትምህርቱ ዘርፍ ተግባራዊ እየሆነ ነው፡፡

Monday, July 9, 2012

Ethiopia፤ የግል ፕሬሱ ለአቅመ አማራጭነት ብቁ ነውን?



ጠቅላላ ሁኔታ
በኢትዮጵያ አንድ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ብቻ ያለ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ የክልል ቴሌቪዥኖችም ቢሆኑ ሙሉ ለሙሉ በመንግስት ይዞታ ስር ናቸው፡፡ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በመንግስት ይዞታ ስር ያሉ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የመንግስት ልሳን ወደመሆኑ አመዝነዋል፡፡ ለግል የተሰጡ  በጣት የሚቆጠሩ የሬዲዮ ጣቢያዎች ቢኖሩም በኤፍ.ኤም. የተወሰኑ ናቸው፡፡ ከኢትዮጵያ ሬዲዮ ውጪ ያለው ብሔራዊ ሬዲዮ ጣቢያ ንብረትነቱ ጥቂት የገዢው ፓርቲ አባላት በመሆኑ ለገዢው ፓርቲ የመወገን አዝማሚያ አለው፡፡ ከዚህ እውነታ በመነሳት ለማንም በማይወግኑ የግል ይዞታዎች ውስጥ የሚገኘው ነፃ ፕሬሱ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ጽሁፍ ‹ነፃ ፕሬሱ ምን ያህል አማራጭ ሚዲያ መሆን ይችላል?› ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት የተለያዩ መስፈሪያዎችን በመጠቀም ለመመለስ ይሞክራል፡፡

ከየካቲት 2001 እስከ ህዳር 2004 ድረስ 224 ያክል የሕትመቶች ውጤቶችን ለማዘጋጀት 211 ድርጅቶች እንደተመዘገቡ የብሮድካስት ባለስልጣን መረጃ ያመለክታል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 137ቱ መጽሔት እና ቀሪዎቹ 87ቱ ጋዜጦች ናቸው፡፡ ከአንድ ክልል በላይ ከሚሰራጩት ሕትመቶች ውስጥ 75 ያህሉ ‹የተቋረጡ/የተሰረዙ›› መሆኑ ተጠቅሷል፡፡ ይሁን እንጂ በገበያ ላይ ከሚውሉት የግል ሕትመቶች መካከል ሳምንታዊዎቹ ሃያ አይሞሉም፡፡ (በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ፡- ሪፖርተር፣ The Reporter፣ አዲስ አድማስ፣ ሰንደቅ፣ ኢትዮ ቻናል፣ ነጋድራስ፣ መሰናዘሪያ፣ ፍትሕ፣ ፍኖተ ነፃነት፣ የኛፕሬስ፣ The Sub Saharan Informer፣ Fortune፣ Capital እና ፕሬስ ዳይጀስት (ሁሉም ሳምንታዊ)፤ ከመጽሔቶች፡- ሙሐዝ (ወርሃዊ)፣ አዲስጉዳይ (ሳምንታዊ) እና አዲስ ታይምስ (ወርሃዊ) - በኢኮኖሚ እና ማሕበራዊ ጉዳዮች የሚያጠነጥኑ ሕትመቶች ናቸው፡፡)

በእንግሊዝኛ የሚታተመውና ንግድና ማስታወቂያ ላይ አተኩሮ የሚሰራው፣ ብቸኛው ዕለታዊ የግል ጋዜጣ The Daily Monitor ይሁን እንጂ ዕለታዊ ስርጭቱ 2000 አይሞላም፡፡ የአገሪቱ ኦፊሴላዊ ቋንቋ በሆነው አማርኛ ቋንቋም ሆነ በሌሎች የክልል ቋንቋዎች የሚታተም አንድም ዕለታዊ፣ የግል ጋዜጣ በአገሪቱ የለም፡፡

የሕትመት ውጤቶቹን ስርጭት በተመለከተ በሚያዝያ ወር፤ 2004 በወጣው መረጃ መሰረት ከፍተኛ ስርጭት ያስመዘገበው ፍትሕ ጋዜጣ ሲሆን ሳምንታዊ አማካዩ 21,750 ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠው አዲስ አድማስ በበኩሉ 12,000 ቅጂዎች አማካይ ስርጭት ሲያስመዘግብ ፕሬስ ዳይጀስት እና መሰናዘሪያ የተባሉት ጋዜጦች 230 እና 960 ዝቅተኛ አማካኝ ቅጂዎችን አሳትመው አሰራጭተዋል፡፡ ከመጽሄቶች ደግሞ አዲስጉዳይ በ20,000 ቅጂ ከፍተኛ ስርጭት አግኝቷል፡፡ ከዚያ በመቀጠል ሎሚ መጽሔት 12,000 ቅጂ በማሰራጨት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ ይህንን መረጃ ያገኝነው ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ሲሆን ትክክልኝነቱን ማረጋገጥ አንችልም:: ምክንያቱም አሳታሚዎቹ የማይስማሙባቸው ቁጥሮች እንዳሉ ሁሉ፣ በመረጃው ላይ የአማርኛውን የእንግሊዝኛ መጽሔት እስከማለት የተደበላለቀ ነገር አለ፡፡ አለመታደል ሆኖ እንጂ እንደ አሜሪካ ባሉ ሀገራት ነጻ የሆኑ እንደ ኒልሰን ሬትንግ ያሉ ሳምንታዊ የሚዲያ ውጤቶችን ተነባቢነትን (Readership) እና ስርጭትን (Circualation) የሚለኩ ኩባንያዎች አሉ:: በርግጥ የሚዲያው ሕልውና በሚያጠራጥርበት ሁኔታ፣ አንባቢ የሚቆጥር ነፃ ኩባንያ ማቋቆም ይከብዳል፡፡

Sunday, July 8, 2012

ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ - አምስት

(ከሰኔ 25፣ 2004 እስከ ሐምሌ 1፣ 2004)

‹‹በኢትዮጵያ ሊትሩ 135ሺህ ብር የሚሸጥ ዘይት ሊመረት ነው›› የሚል ዜና ይዞ የወጣው መሰናዘሪያ ጋዜጣ ነው፡፡ ‹‹…ቴራ የተባለ የጀርመን ካምፓኒ [ባሕርዳር] ከነሐሴ ወር ጀምሮ ሊትሩ 7,500 ዶላር የሚሸጥ ዘይት እያመረተ ለውጭ ገበያ እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡….››

** ** **
‹‹ዲግሪ ያላቸው ዜጎች የጎዳና ተዳዳሪዎች ሆነዋል››  የሚል አስደንጋጭ መርዶ ያስነበበው ሪፖርተር ጋዜጣ በረቡዕ እትሙ ነው፡፡ ‹‹ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ የማስተርስና የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ዜጎች አዲስ አበባ ውስጥ የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎች ሆነው መገኘታቸው ተጠቆመ፡፡

‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ… የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎች ወደ መልካም ሕይወት ለመመለስ፣ … በማድረግ ላይ ባለው እንቅስቃሴ መምህር፣ ነርሶችና በተለያዩ ሙያዎች የተመረቁ ዜጎች የጎዳና ላይ ተዳዳሪ ሆው መገኘታቸውን አረጋግጧል….››

** ** **

‹‹ይቅርታ›› የኢሕአዴግ ቃጭል? ወይስ… ያለው ተመስገን ደሳለኝ ፍትህ ጋዜጣ ላይ ነው፡፡ ‹‹…እነሆም ማሰር፣ ከአሰሩ በኋላ በይቅርታ መልቀቅ፣ ከለቀቁ በኋላ ደግሞ ይቅርታን አንስቶ መልሶ ማሰር…‹በይቅርታ ተቀባዩ አንገት ላይ ተንጠልጥሎ ቀሪ ዘመንን በሞላ ‹ኪሊ፣ ኪል…› የሚል ‹ቃጭል› ነው›…››

Saturday, July 7, 2012

የኪራይ ሰብሳቢ ማዕበል

በዘላለም ክብረት
“Rent-seeking may, indeed, impose costs to the economy as high, if not higher, than those arising from corruption.”
  Anthony Ogus , Corruption and Regulatory Structures.

ገንዘብን መግዛት (Rent seeking)

በስነ ምጣኔ ሳይንስ ከእያንዳንዱ ኢኮኖሚ ጀርባ ብዙ ጋሬጣዎች(Economic Inefficiencies) ሊኖሩ ይችላሉ ለምሳሌ እንደ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት፣ የገንዘብ እና የፊስካል ፖሊሲ ክፍተት፣ ሙስና ፣ ገንዘብን መግዛት (Rent seeking) ወ.ዘ.ተ ናቸው፡ ከነዚህ የኢኮኖሚ ማነቆዎች ውስጥ ገንዘብን መግዛት (Rent seeking) የተባለውን ስንመለከት፡፡በአጠቃለይ ኢኮኖሚስቶች ‹‹እሴት አልባ ትርፍ ወይም አሁን ያለው ገንዘብ በራሱ ያለምንም ዕሴት ማጎልበት ተጨማሪ ገንዘብ እንዲገዛ ለዛ መበርታት›› ብለው ይተረጉሙታል፡፡

John Mbaku የተባሉ ኢኮኖሚስት ‘Corruption and Rent-seeking’ ባሉት ፅሁፋቸው ገንዘብን መግዛትን ‹‹የመንግስት ፖሊሲዎችን ውጤት ለማስቀየር የሚደረግ እንቅስቃሴ›› ብለው ይተረጉሙታል ፡፡ የገንዘብን መግዣ ድርጊቶች ስንመለከት የተያዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡

Anne Kruger የተባሉ የሚኒሶታ ዩንቨርስቲ ኢኮኖሚስትThe Political Economy of Rent-Seeking Economy’ ባሉት ፅሁፋቸው ‹‹ገንዘብን ለመግዛት የሚደረገው ውድድር አንዳንዴ ንፁህ እና ህጋዊ በሆነ መልኩ አንዳንዴ ደግሞ እንደ ሙስና፣ ጥቁር ገበያ እና ህገወጥ የዕቃ ማስተላለፍ ያሉትን ህገወጥ መንገዶች በመጠቀም ሊከናወን ይችላል›› ይላሉ፡፡ ይሄም ገንዘብን መግዛት ሁሌም ህገወጥ ተግባር ብቻ አይደለም ወደሚለው መደምደሚያ ያደርሰናል ማለት ነው፡፡

Wednesday, July 4, 2012

አባይን መልሱልኝ!

በሶልያና ሽመልስ

አባይ……. አባይ……..  አባይ…….. አባይ
የአገር አድባር  ያገር ኩራት ……..የአገር  ሲሳይ


ቲቸር ታደሰ ከማልረሳቸው  የአንደኛ ደረጃ መምህራን መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ታዲያ የስድስተኛ ክፍልን የህብረተሰብ ትምህርት ለየት የሚያደርገው የቲቸር ታደሰ ከክፍል ሥራ እና ከንባብ በተጨማሪ ይዘዋቸው ይመጡ የነበሩት ከክፍለ ጊዜው ጋር የተገናኙ ጨዋታዎች እና የጠቅላላ እውቀት ጥያቄዎች ነበሩ፡፡ ታሪክ ቀመስ ትረካዎችን ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ሲያነቡልንም አስታውሳለሁ፡፡ (አዲስ ዘመንም የሚነበብ ታሪክ የሚጽፍበት ወቅት ነበረው ማለት ነው?) ታዲያ በአብዛኛዎቹ ክፍለ ጊዜዎች መጨረሻ ላይ ስለቀድሞ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ታሪክ እና ስለተያያዥ ጉዳዮች ሲያወሩ የአባይ ጥቅም ላይ አለመዋልን  በቁጭት ማንሳታቸው አይቀርም ነበር፡፡
ከሚሽነሪ ት/ቤቱ ጥብቅ ሃይማኖታዊ ስነ ስርዓት  በመነሳት ምንም አይነት መንፈሳዊ ያልሆነ ሙዚቃ መዝፈን የሚያስቀጣ ቢሆንም ቲቸር ታደሰ ግን በኅብረተሰብ ትምህርት በሬድዮ  ክፍለ ጊዜ ማጠናቀቂያ ላይ በተደጋጋሚ የሚመጣውን፤
አባይ……. አባይ……..  አባይ…….. አባይ
የአገር አድባር ያገር ኩራት ……..የአገር  ሲሳይ

በጋራ እንድንዘምር ይፈቅዱልን ነበር፡፡ የኅብረተሰብ ትምህርት እና ልጅነት ሲነሳ አብሮኝ የሚከሰተው የአባይ ትዝታን የምጋራው እኔ ብቻ ነኝ ብዬ አላስብም፡፡ ዓይነቱ የተለየ ቢሆንም  ሰለአባይ ስንማር  እና ሲነገረን  የኖርናቸውን ነገሮች በማስታወስ የአንደኛ ደረጃ የህብረተሰብ ትምህርቱ  እና የአባይ  ትውስታ የሚቀላቀልበት የኔ ቢጤ ወዳጅ መቼም አላጣም፡፡


የአሁኑ አባይ የማን  ነው?

GTP የት አደረሰን?

በናትናኤል ፈለቀ

የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የሁለተኛው የ5 ዓመት የልማት ስልታዊ እቅድ (Plan for Accelerated Development to End Poverty, PASDEP) ጊዜ ገደብ መገባደዱን ተከትሎ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በኖቬንበር ወር 2010 ዓም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን ይሁንታ ካገኘ በኋላ ነበር የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክሪያሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ሦስተኛ የ5 ዓመት ስልታዊ ዕቅድ ሆኖ መተግበር የጀመረው:: የትግበራው ዋነኛ ግብ የተጀመረው በሁለተኛው የ5 ዓመት የልማት ስልታዊ ዕቅድ አተገባበር ላይ ለተከታታይ ዓመታት ኢኮኖሚው ያስመዘገበውን ፈጣን ባለሁለት አሃዝ እድገት በማስቀጠል የኢንደስትሪው ዘርፍ የኢኮኖሚውን መሪነት ሚና ከግብርና የሚረከብበትን ቅድመ ሁኔታ ማመቻቸት  ነበር::

ይህ ዕቅድ ይፋ ከሆነበት ጊዜ አንስቶ ከየአቅጣጫው የተቃውሞ ትችቶችን ለማስተናገድ ተገዷል:: ዕቅዱ ላይ የሚቀርቡት ትችቶች በዋነኛነት የሚያጠነጥኑት በሁለት አንኳር ጉዳዮች ላይ የነበረ ሲሆን የመጀመሪያው የትችቶች ማጠንጠኛ የመንግስትን ቅጥ ያጣ ጉጉነት የተመለከተ ሲሆን መደገፊያ መከራከሪያውም ዕቅዱ ውስጥ እንደሚተገበሩ የታቀዱትን ተግባራትን ለመከወን የሚያስፈልገውን ያህል ገንዘብ ለማግኘት እንደሚያስቸግርና ዕቅዱ የመንግስትን የመፈፀም አቅም በእጅጉ አጋኖ ያቀረበ ነው የሚል ነበር፡፡ ሁለተኛው ትችት ሆኖ የቀረበው ደግሞ የዕቅዱ አተገባበር ከፍተኛ የሆነ የመንግስት ወጪ ስለሚፈልግ ቀድሞውንም ቢሆን ለቁጥጥር ላስቸገረው ምጥቀ ግዥበት (Hyper Inflation) በዕንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ይሆናል ከሚለው ፍራቻ ነበር፡፡

Sunday, July 1, 2012

ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ - አራት

(ከሰኔ 18፤ 2004 እስከ ሰኔ 24፤ 2004)

‹‹የኢሕአዴግ የስለላና የቁጥጥር መዋቅር ከ1 ለ 5 ወደ 1 ለ 11 አደገ›› የሚል ዜና ይዞ የወጣው ፍኖተ ነፃነት ነው፡፡ በዝርዝሩም ‹‹… ታማኝ ውስጥ አዋቂዎች እንደሚሉት ‹በቅርቡ ፖሊሶች፣ የመንደር ካድሬዎችና ደህንነቶችን የከተማውን ነዋሪ ቅጽ እያስሞሉ ናቸው፡፡ ከዚያም 1 ለ 11 በማደራጀት እያንዳንዱን የከተማ ነዋለሪ ለመቆጣጠር ታቅዷል፡፡›…››

* * *


ዕንቁ መጽሔት በለጠ ደምሴ ከተባለ ከፊል ከተሜ፣ ከፊል ገጠሬ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ስለራሱ እና ስለሚኖርበት ማሕበረሰብ ሥራ የማይሰራቸው በዓላት ሲናገር ‹‹…በ5 አቦን፣ በ7 ሥላሴን፣ በ12 ሚካኤልን፣ በ13 እግዚአብሔርአብን፣ በ16 ኪዳነ ምህረትን፣ በ19 ገብርኤልን፣ በ21 ማርያምን፣ በ23 ጊዮርጊስን፣ በ24 ተክለሃይማኖትን፣ በ27 መድኃኔዓለምን፣ በ29 ባለወልድ፣ በ30 ዮሐንስን አንሠራም፡፡…ቅዳሜ እና እሁድም አሉ፡፡ …›› ብሎ አስገራሚ ቃለ ምልልስ አድርጓል፡፡

* * *


ሪፖርተር ጋዜጣ ‹‹የመንግስት አመራሮች ለውጥን የመምራት ክህሎት አለማዳበራቸው ተገለጸ›› ባለበት የረቡዕ እትሙ