Monday, December 5, 2016

የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች ለ48ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

አምስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች፣ ሶልያና ሽመልስ (በሌለችበት)፣ በፍቃዱ ኃይሉ (ከእስር ቤት)፣ አጥናፉ ብርሃኔ፣ አቤል ዋበላና ናትናኤል ፈለቀ ነገ ማክሰኞ ሕዳር 27፣ 2009 ለመጨረሻ የይግባኝ ብይን ይቀርባሉ፡፡ ሰባት የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችና ሶስት ጋዜጠኞች ከታሰሩበት ሚያዚያ 17፣ 2006 ጀምሮ በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት እየቀረቡ ቆይተው አምስት ተከሳሾች ከሳሽ የፌደራል ዓቃቤ ሕግ ያቀረበውን ክስ አንስቻለሁ በማለቱ ሐምሌ 01፣ 2007 የተፈቱ ሲሆን አራቱ ተከሳሾች ደግሞ ነፃ ናቸው ተብለው ጥቅምት 5፣ 2008 ከእስር ተለቀዋል፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪ የሆነው በፍቃዱ ኃይሉም የቀረበበት ክስ ከፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ ጋር የማይገናኝ በመሆኑ በመደበኛው የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257/ሀ መሰረት በጽሁፍ አመፅ የመቀስቀስ መተላለፍን ፈፅሟል፣ ይሄንም ይከላከል ተብሎ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በጥቅምት 10፣ 2008 በተሰጠው ውሳኔ መሰረት በሃያ ሽህ ብር ዋስትና ከእስር መለቀቁ ይታወቃል፡፡

በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ሶልያና ሽመልስ ፣ አቤል ዋበላና አጥናፉ ብርሃኔ

ነገር ግን የፌደራል ማዕከል ዓቃቤ ሕግ በታሕሳስ 04፣ 2008 በተፃፈ ይግባኝ ‹በከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሳኔ ቅር ተሰኝቻለሁ፣ ተከሳሾቹ በነፃ መሰናበት የለባቸውም› በማለት ባቀረበው ይግባኝ መሰረት ላለፍት አስራ ሁለት ወራት በስር ፍርድ ቤት የመጨረሻ ውሳኔ ያልተሰጠበት በፍቃዱ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት በመቅረብ ክሳቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ሲሆን በነገው ዕለትም ለ50ኛ ጊዜ የስር ፍርድ ቤቱ ውሳኔን ለማፅናት ወይም ለመሻር በሚሰየመው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡


በሌላ በኩል ደግሞ ጦማሪ በፍቃዱ ኃይሉ ጥቅምት 18፣ 2009 አየር ላይ ለዋለው የአሜሪካን ድምፅ (Voice of America) ‹የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አጥላልተሃል› በሚል አርብ ሕዳር 02፣ 2009 ከመኖሪያ ቤቱ ተይዞ የታሳረ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን፤ እስከ አሁን ድረስ ፍርድ ቤት ያልቀረበ ከመሆኑም በላይ በአሁኑ ወቅትም ‘በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ’ እንደሚገኝ ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ ጠበቃም ሆነ የቤተሰብ አባልም መጠየቅ እንደማይችል የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ በነገው የፍርድ ሒደትም የመቅረቡ ጉዳይም እንዲሁ አጠያያቂ ነው፡፡

Thursday, October 20, 2016

A year after their release, Zone 9 Bloggers will reappear to Court

Four of the Zone 9 bloggers,  Abel Wabella,  Atnafu Berhane, Befkadu Hailu and Natnael Feleke will reappear to the Federal Supreme Court, tomorrow October21, 2016 for a verdict and Soliana Shimelis’s case will continue to be entertained in absentia.


Natnael Feleke (left top), Befkadu Hailu (right top), Abel Wabella (left bottom), Atnafu Birhane (right bottom) and Soliyana Shimelis (middle)
After their arrest on April 2014, the bloggers were charged with terrorism and the Federal High Court which has a first instance jurisdiction over the case acquitted them. However, the Federal Public Prosecutor appealed against the decision of the lower court and the Federal Supreme Court, a higher court with an appellate jurisdiction over the matter accepts its appeal.

On tomorrow's trial, the court is expected to give a final verdict over the oral argument the defendants and the prosecutor presents in addition to a verdict on the documentary evidences presented against the Bloggers. If the court accepts the prosecutor's appeal, the case will send back to the Federal High Court and the trial will resume while the bloggers rearrested.

On the other hand, one of the bloggers, Befkadu Hailu had still a pending case with the same cause of action under a lenient charge at the Federal High Court and Natnael Feleke also had a pending case in which he is alleged of incitement by talking politics.  

Saturday, October 15, 2016

ሰ.መ.ጉ. 25ኛ ዓመቱን እያከበረ ነው፤ የዜጎች ድጋፍ ያስፈልገዋል!

(በፍቃዱ ዘ. ኃይሉ)

በአገራችን ብቸኛው ሰብኣዊ መብት ላይ አተኩሮ የሚሠራው መንግሥታዊ ያልሆነ የሰብኣዊ መብቶች ጉባኤ (ሰ.መ.ጉ.) ከተመሠረተ 25 ዓመታት ሞሉት፡፡ ቀድሞ የኢትዮጵያ ይባል የነበረው ኢ.ሰ.መ.ጉ. በበጀት እጦት ምክንያት በ3 ክልሎች ብቻ ጽሕፈት ቤቶች ስለነበሩት ሰ.መ.ጉ. ለመባል ተገዶ ከርሟል፡፡ ይሁን እንጂ በቅርቡ ለማገገም እያደረገ ባለው ጥረት የጽሕፈት ቤቶቹን ቁጥር 6 አድርሶ የቀድሞ ሥሙን ለማስመለስ እና ሥራውንም በአገሪቱ ክልሎች በሙሉ ለማድረስ እየሞከረ ነው፡፡ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ብፅአት ተረፈ ዛሬ (ቅዳሜ፣ ጥቅምት 5፣ 2009) ከወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፣ ‹በተለይ ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ በርካታ ባለሙያዎቻቸውና መረጃዎቻቸው ልክ ሕገ መንግሥቱን በኃይል ለመናድ የተንቀሳቀሱ በማስመሰል በመነገሩ፣ ተቋሙን ጥለው እንዲሰደዱ በማድረግ ተዳክመው ቆይተዋል፡፡ ሌላው በ2001 የወጣው የበጎ አድራጎት ድርጅቶች አዋጅ ተፅዕኖ አሳርፎባቸዋል፡፡ በተለይ በጀት ከውጭ አለማግኘታቸው ጽ/ቤቶቻቸውን እንዲዘጉና በርካታ ሠራተኞቻቸውን እንዲቀንሱ አድርጓቸዋል፡፡›

Tuesday, October 11, 2016

The 2016 Martin Ennals Award Laureate is announced


 Ilham Tohti was selected by a jury of 10 global Human Rights organizations as the 2016 Martin Ennals Award Laureate. The Award is given to Human Rights Defenders who have shown deep commitment and face great personal risk. The aim of the award is to provide protection through international recognition. Strongly supported by the City of Geneva, the Award will be held on October 11th, 16:00 Ethiopian time.

The Laureate: Ilham Tohti (China)

Ilham Tohti has worked peacefully for two decades to foster dialogue between Uyghurs and Han Chinese. He has been subject to official surveillance and harassment since 1994. On January 15, 2014, Ilham Tohti was arrested on charges of separatism and terrorism and sentenced to life imprisonment after a two-day trial.



In addition to Ilham the two other finalists who received Martin Ennals Prizes; these are:

Razan Zaitouneh (Syria) 

Razan has dedicated her life to defending political prisoners, documenting violations, and helping others free themselves from oppression. She founded the Violations Documentation Center (VDC), which documents the death toll and ill-treatment in Syria's prisons. She had started to cover all sides in the conflict when she was kidnapped, alongside with her husband and two colleagues, on 9 December 2013. Her whereabouts remain unknown.

Zone 9 Bloggers (Ethiopia)

Kality prison in Ethiopia has 8 zones and holds many journalists and political prisoners. 9 young activists called themselves ‘Zone 9’ as a symbol for Ethiopia as a whole. They document human rights abuses and shed light on the situation of political prisoners in Ethiopia. Six of its members were arrested and charged with terrorism. Although they have now been released, three are in exile while four of the six remaining in Ethiopia are still facing charges and are banned from travel.

Zone 9 wants to congratulate the winner of the award and hope the award will have an impact on securing the release of Illham. We wish him best of luck in the future.


የማርቲን ኤናልስ ሽልማት የ2016 ሎሬት ታወቀ


10 ዕውቅ የዓለም የሰብኣዊ መብቶች ድርጅቶች የሚያዘጋጁት ዓመታዊው የማርቲን ኤናልስ የሰብዓዊ መብት የ2016 የመጨረሻ ሦስት ዕጩዎች መካከል ዞን 9 የጦማሪዎች እና አራማጆች ስብስብ አንዱ መሆኑ ግንቦት ወር ላይ መገለጹ ይታወሳል፡፡ ከዞን 9 በተጨማሪ የእድሜ ልክ እስራት ፍርደኛው ቻይናዊው ኢልሃም ቶቲ እና በሶሪያ አማፅያን የተጠለፈችው ሶሪያዊቷ ራዛን ዛይቱን መታጨታቸው ይታወቃል፡፡

ዛሬ አመሻሹ ላይ ይፋ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው አሸናፊ ኤ.ኤፍ.ፒ. የተባለው የዜና ወኪል ቀድሞ አሸናፊውን በመግለጹ ማርቲን ኤናልስም ይፋ እንዲሆን አድርጓል፡፡ በዚህም መሰረት ቻይናዊው የዊጉር ሕዝብ የመብት ታጋይ ኢልሐም ቶቲ የዚህ ዓመት ሎሬት በመሆን ተመርጧል፡፡ የሽልማት ስነስርዓቱ ዛሬ ምሽት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከአንድ ሰዓት ጀምሮ ይከናወናል፡፡
የመጨረሻ ዕጩዎቹ አጭር መግለጫ

አሸናፊው፤ ኢልሃም ቶቲ (ከቻይና)

ኢልሃም ቶህቲ በዊጉር እና ሃን ቻይኖች መካከል ጤናማና ሠላማዊ ውይይት እንዲዳብር ለሁለት ዐሥርት ዓመታት የደከመ ምሁር ነው፡፡ እ.ኤ.አ. ከ1994 ጀምሮ በሚጽፋቸው ጽሑፎች ምክንያት ከፍተኛ የመንግሥት ክትትል እና እንግልት የገጠመው ሲሆን በጃንዋሪ 15፣ 2015 በከፋፋይነት ክስ እና በሁለት ቀን ችሎት የዕድሜ ልክ እስር ተፈርዶበታል፡፡



በተጨማሪም የሚከተሉት የመጨረሻ ዕጩዎች ሽልማቶችን ተቀብለዋል፡፡

ራዛን ዛይቱን (ከሶሪያ)

ራዛን ሕይወቷን ሙሉ የፖለቲካ እስረኞችን፣ የመብት ጥሰቶችን እና ሌሎች ራሳቸውን ነጻ እንዲያወጡ በመርዳት የኖረች ሰው ነች፡፡ የመብት ጥሰቶች መመዝገቢያ ማዕከል (ቪዲሲ) አቋቁማ በሶሪያ ያሉ እስረኞች ላይ የሚደርሱ እንግልቶችን እና የሞት እንዲሁም የመሰወር ዝርዝሮችን እየመዘገበች ይፋ አድርጋለች፡፡ ራዛን በዲሴምበር 9፣ 2013 ጭምብል ባጠለቁ ሰዎች ከሁለት ባልደረቦቿ እና ባለቤቷ ጋር ከቢሮዋ ታግታ ከተወሰደች በኋላ እስካሁን የት እንዳለች አይታወቅም፡፡ የዞን 9 ጦማሪያን እና አራማጆች ስብስብ

የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና አራማጆች ስብስብ (ከኢትዮጵያ)

ቃሊቲ ማረሚያ ቤት 8 ዞኖች አሉት፡፡ ዞን 9 በሚል ሥም የተሰባሰቡት ወጣት ጦማሪዎች የጦማሩን መጠሪያ ያገኙት ኢትዮጵያ ሰብኣዊና ፖለቲካዊ መብቶች የተገደቡባት ትልቅ እስር ቤት ናት ከሚለው ነው፡፡ የዞን 9 ጦማሪያን የሰብኣዊ መብት ጥሰትን እና የፖለቲካ እሰስረኞች ሁኔታ ምን እንደሚመስል ለማሳየት ይጽፋሉ፡፡ ስድስቱ የስብስቡ አባላት ታስረው የተፈቱ ሲሆን፣ ሦስቱ አሁን በስደት ላይ ናቸው፡፡ ታስረው ከተፈቱት ውስጥ አራቱ ይግባኝ ተብሎባቸው እና የመንቀሳቀስ መብታቸው ተገድቦ ፍርድ ቤት እየተመላለሱ ነው፡፡


ዞን 9 ለሽልማቱን አሸናፊ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ፣ ሽልማቱም ኢልሐም እንዲፈታ ጫና ያሳድራል ብሎ ያምናል፡፡ ለወደፊቱ መልካም ዕድል እንዲገጥመው ይመኛል፡፡ 

Wednesday, October 5, 2016

Zone 9 Blogger, Natnael Feleke Arrested

Yesterday October 04, 2016 Natnael Feleke, a Zone 9 Blogger and two of his friends, Tsedeke Digafe and Addisalem Mulugeta are taken detention. The reason given by the police about their arrest is while sitting at Lalibela Restaurant and talking loudly about the death of hundreds on Sunday, October 02, 2016 at the yearly Thanksgiving ceremony in Bishoftu, Ethiopia and blaming the government for the deaths occurred, they uttered seditious remarks in a public place.
Natnael and his friends brought to the Federal First Instance court, Kera Branch Criminal Bench this morning and the judge adjourned them for tomorrow October 06, 2016 to give a decision on the bail issue.

Natnael Feleke

We at the Zone 9 are deeply saddened by this news that Ethiopia is becoming a country citizens can’t even discuss anything political. Thus, we request the Ethiopian government to release Natnael and two of his friends unconditionally.

የዞን ዘጠኝ ጦማሪው ናትናኤል ፈለቀ ታሰረ


የዞን ዘጠኝ ጦማሪው ናትናኤል ፈለቀ ትናንት ማክሰኞ መስከረም 24፣ 2009 ከስራ ሰዓት በኋላ ጸደቀ ድጋፌ እና አዲስአለም ሙሉጌታ ከተባሉ ሁለት የስራ ባልደረቦቹ ጋር በተለምዶ ‹ስታዲየም› ተብሎ የሚታወቀው አካባቢ በሚገኝው ‹ላሊበላ› ሬስቶራንት ውስጥ ተቀምጠው “ጮክ ብለው ‘የቢሾፍቱ ጭፍጨፋ የመንግስት ጥፋት ነው’፣ ‘እያሸበረ ያለው ራሱ መንግስት ነው’ በማለት አውረተዋል”፤ በሚል ምክንያት በፖሊስ ተይዞ ታሰረ፡፡ ናትናኤል እና ጓደኞቹ ዛሬ መስከረም 25፣ 2009 ጠዋት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቄራ ምድብ የወንጀል ችሎት ቀርበው የዋስትና ጉዳይ ለማየት አሻራ ይስጡና ነገ መስከረም 26፣ 2009 በድጋሚ እንዲቀርቡ ታዘው ወዳረፉበት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የካዛንችስና አካባቢው ፖሊስ ጣቢያ (በተለምዶ 6ተኛ እየተባለ የሚታወቀው) ተመልሰዋል፡፡

Natnael Feleke

ዞን ዘጠኝ አቋም

የናትናኤል እና የጓደኞቹ እስር አሁን አገሪቱ እየሔደችበት ያለውን መንገድ በሚገባ ያሳያል፡፡ ኢትዮጵያ ከጓደኞች ጋር ሰብሰብ ብለው የፖለቲካ ጉዳይ ማውራት የሚያሳስርባት አገር መሆኗም ለሁላችንም አሳዛኝ ነው፡፡ ስለዚህም ናትናኤልና ጓደኞቹ ሰውነታቸው ያስገኝላቸውን ሃሳባቸውን የመግለፅ መብታቸውን ከመጠቀማቸው ባለፈ ቅንጣት ታክል የሕግ መተላለፍ ያልፈፀሙ በመሆኑ አሁኑኑ ይፈቱ ዘንድ እንጠይቃለን፡፡

Monday, September 19, 2016

ማኅበራዊ ሚዲያው እና የመንግሥት ስጋት



በተስፋዬ ዓለማየሁ

የማኅበራዊ ሚዲያውን አጠቃቀም በተመለከተ ተከታታይ ዘመቻዎች እና ማጥላላቶች በተለያዩ ግዜያት በሕትመት ሚዲያው ሳነብ፣ በብሮድከስት ሚዲያውም ሳደምጥ ቆያቻለሁ፡፡ እነዚህን የአጠቃቀም ጉድለቶች ላይ ያተኮሩ ዘመቻዎች ታዲያ እንደ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ስመለከታተቸው ነው የሰነበትኩት፡፡ ምክንያቱም መሰል ፈራጅ ዘጋቢ ፊልሞች በሕትመት ሚዲው ላይ ይሠሩ እና ጠንከር ያለው እርምጃ ይከተል ስለነበር ነው፡፡ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ዙሪያ በመጀመሪ የኮረኮረኝ ጽሑፍ "ከማኅበራዊ ሚዲያው በስተጀርባ" በሚል ርዕስ በሪፖርተር ገዜጣ ላይ ከወጣ በጣም ቆየት ብሏል፡፡  የጽሑፉ ዋና ዓላማ የነበረው ከማኅበራዊ ሚዲያ ጠቀሜታ ‹በስተጀርባ ያለውን አደጋ ነው ማመመልከት› ነበር፡፡ የጽሑፉ አዘጋጅም በሚገባ አስረጅ ምሳሌዎችን አስቀምጠው ጠቀሜታውንም ለመዳሰስ ሞክረው ጽሑፋቸውን ቢያበቁም፣ ከዚያ በኋላ በተከታታይ እንዲሁ በተለያዩ ግዜያት ቅኝታቸው ማኅበራዊ ሚዲያው ከጥቅሙ ባሻገር ጉዳቶቹ ላይ ያተኮሩ ጽሑፎችን አንብቤያለሁ፡፡ እርግጥ ነው በተነሱት ሐሳቦች ዙሪያ የማኅበራዊ ሚዲያው፣ በዋነኛነትም ፌስቡክ ከጥቅሙ በዘለለ ባሉት አሉታዊ ተፅዕኖዎች ላይ መሠረታዊ ልዩነት ከጸሐፊዎቹ ጋር የለኝም፡፡ "የጥላቻ ንግግሮችን ማስተላለፊያ ነው""አሉባልታ ማሰራጫ ነው""የሠራ ግዜን ይሻማል"፣ "በቅርባችን ካሉ ወዳጅ ጓደኞቻቸችን ጋር ይለያየናል"፡፡ ሌሎችም የፌስቡክ እንከኖችን እያስታወስን መዘርዘር አንችላለለን፡፡
  
ማኅበራዊ ሚዲያው ግን በርካታ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ልንዘነጋው አይገባም፡፡ የማኅበራዊ ሚዲውን ችግሮች ማሳየቱ ለተጠቃሚው አጠቃቀሙን እንዲፈትሽ ስለሚያደርጉ መልካም ሊባል ቢሆንም፡፡ ችግሮቹን ማጉላቱ ላይ ግን አልስማማም፡፡ ከሚጠቀሱት ችግሮች ውስጥ ለራሳችን በጣም ተስማሚ የሆኑ ችግሮች አይጠፉምና በአግራሞት ወይም በድንጋጤ "ይህማ የእኔም ችግር ነው" የምንለው እና ለችግሩም ተጋላጭ እንደሆንን፣ በደንብ እንዲሰማን የሚያደርጉን ማሳያዎች ስለሚዘረዘሩ ሊያሸማቅቁን ይችላለሉ፡፡ ይህንን ስሜት ከመፍጠር ተሻግረው ግን በሕትመት ሆነ በብሮድካስት ሚዲያ የሚተላለፉት መልዕክቶች ውጤታቸው  (ኢፌክታቸው) ምን ያህል እንደሆነ ትዝብቱን ለየግላች ልተወውና፣ ማኅበራዊ ሚዲያው ንበማስተዋል መጠቀም የሚለው ምክር ላይም እንስማማና፣ ፌስቡክ በአሁኑ ሰዐት ሁነኛ አማራጭ ሚዲያ እንደሆነ ለማሳየት የሚከተለውን እጽፋለሁ፡፡

መነሻ፤ በአገራችን የሕትመት እና የብሮድካስት ሚዲያ ሁኔታ ወፍ በረር ቅኝት

በአገራችን ውስጥ ያለት የብሮድካስት እና ሕትመት ሚዲያዎች ከሚጠበቅባቸው አንፃር ብዙ ይቀራቸዋል፡፡ በአግባበቡ እያገለገሉን አይደለም፡፡ ለዚህም በርካታ ምክንያቶችን ልንደረድር እንችላለለን፤ የጋዜጠኞች ብቃት ማነስ፣ የጋዜጠኞች የሥነ ምግባር ጉድለት፣ የጋዜጠኞች እና የሚዲያ ባለቤቶች የፖለቲካ ፍላጎት እና አመለካከከት፣ የገበያው ትርፋማነት እያልን በርካታ ምክንያቶችን ብንደረድርም "የእናቴ መቀነት…" ከመሆን አይዘልም፡፡  ምክንያቱም በእነዚህ ሰበቦች ወይም ችግሮች ውስጥ እንኳን የጋዜጠኝነት መርሖዎችን ለማክበር ከመሞከር ይልቅ ሲጥሷቸው በግልጽ ይስተዋላሉ እና ነው፡፡ በተለይም ደግሞ ጠንከር ባሉ ሁሉን ዐቀፍ ተሳትፎ እና ውይይት በሚፈልጉ አገራዊ፣  ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ሁሉንም በዕኩል ደረጃ አያሳትፉም አያገልግሉም፡፡ አብዛኛዎቹ የአገራች ሚዲያዎች በጣም የተካኑባቸው እና የሚሽቀዳደሙባቸው ዘገባዎች በጣም ለስለስ ያሉ ማኅበራዊ፣ የመዝናኛ እና የስፖርት፣ የኪነ ጥበብ፣ የፊልም እና የፋሽን ጉዳዮች ናቸው፡፡

Friday, September 16, 2016

በይነመረብ እና አፋኝ መንግሥታት


ኢንተርኔት ወይም በይነመረብን በየቀጠናው እና በየመተግበሪያው ዓይነት ብልጭ ድርግም በማድረግ የመረጃ ፍሰትን በሚፈልገው መልኩ ለመቆጣጠር ይፋዊ እንቅስቃሴ የጀመረውን የኢትዮጵያ መንግሥት የበይነመረብ ቁጥጥር (censorship) አካሔድ በመታዘብ አጥናፉ ብርሃኔ አገራችን ውስጥ ያለውን የበይነመረብ አፈና ከዓለምዐቀፍ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማነጻጸር በዚህ መጣጥፉ ግልጥልጥ አድርጎ ያሳየናል

አፋኝ ወይስ አዳኝ?

በ2014 (እ.ኤ.አ.) በቱርክ አንካራ ከመናገር ነጻነት መብት ተቆርቋሪ ድርጅቶች ‹Committee to Protect journalists› (ሲ.ፒ.ጄ.) እና ‹International Press Institute› (አይ.ፒ.አይ.) ጋር ስብሰባ የተቀመጡት ጋዜጠኞችን በማሰርና የተለያዩ ሚድያዎችን በማፈን የሚታወቁት የቱርኩ መሪ ሪሴፕ ጣይብ ኤርዶሃን ለብዙዎች አማራጭ ሚዲያ እየሆነ የመጣውን የማኅበራዊ ሚድያ ወይም ኢንርኔትን (በይነመረብ) አንደሚጠሉ በግልጽ ተናግረው ነበር።

ኤርዶሃን ይህን ከተናገሩ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በገዛ ወታደሮቻቸው መፈንቅለ መንግሥት ተሞከረባቸው። የቱርክ ወታደሮች ከካምፓቸው ወጥተው የቱርክ መንግሥት አፈቀላጤ የሆነውን የቱርክ ራዲዮ ጣብያና ቴለቭዥን ማሰራጫን (TRT) ተቆጣጠረው፣ የመፈንቅለ መንግሥቱን ዜና አወጁ። ኤርዶሃን ይህን እርምጃ አውግዘው ደጋፊዎቻቸውን ለማሰባሰብ ጊዜ አልፈጀባቸውም። ከሁለት ዓመት በፊት “ጠላቴ” ብለው የፈረጁት በይነመረብ (ኢንተርኔት) ሥልጣናቸውንና ሕይወታቸውን ለማዳን ብቸኛ አማራጫቸው ነበር።

በቱርክ መፈንቅለ መንግሥት አድራጊ ወታደሮች የተረሳው የአገሪቱ የቴሌኮም አገልግሎት አቅራቢ በኤርዶሃን ታማኝ ደጋፊዎች እጅ ስለነበር በይነመረብን ተጠቅመው ሕዝቡ “የቱርክን ዴሞክራሲ” ከመፈንቅለ መንግሥት ለመከላከል አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን እንዲያሰማ ከተደበቁበት ቦታ ሆነው ነበር ብሔራዊ ጥሪ ያቀረቡት። የሚድያ ጠላት ተብለው የሚፈረጁት ኤርዶሃን መፈንቅለ መንግሥት እየተደረገ ባለበት ሰዐት ደጋፊዎቻቸውን ለማስሰባሰብ በበይነመረብ ከቲውተር (Twitter) እስከ ፌስታይም (Facetime)  የተጠቀሙ ሲሆን በአንድ ወቅት በቱርክ መንግሥት ከፍተኛ የታክስ ቅጣት የተጣለበት ዶሃን ሚድያ ግሩፕ (Doğan Media Group) እና የታይም ዋርነር (Time Warner) ጥምረት የሆነው ሲ.ኤን.ኤን. ተርክ (CNN Turk) የዜና ተቋም ጋር በቀጥታ በአይፎን ስልክ የሚሠራውን ፌስታይም (Facetime) አፕሊኬሽን በመጠቀም ቃለ ምልልስ አርገው ሕዝባቸው ለመፈንቅለ መንግሥቱ እንቢታውን እንዲገልጽ ብሔራዊ ጥሪ በማድረግ የታንክን አፈሙዝ በበይነመረብ ወይም ኢንተርኔት ጠምዝዘው ሕይወታቸውንም ሥልጣናቸውንም ከአደጋ ታድገዋል።

በይነመረብ ሥልጣን አልለቅ ብለው ወንበር ላይ ዐሥርት ዓመታትን ሙጭጭ ብለው ለተቀመጡ አምባገነን መሪዎች ጠላት ነው። በቅርቡ በኡጋንዳ በተደረገው አገራዊ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ወቅት “ምርጫው ሠላማዊና የተረጋጋ ሆኖ እንዲጠናቀቅ” ወይም  በትክክለኛው ትርጉሙ፣ የተቃዋሚ ኃይሎችን ድምፅ ለማፈን የዩጋንዳ መንግሥት የወሰደው እርምጃ ማኅበራዊ ሚድያዎችንና የአጭር ጽሑፍ መለዋወጫ መተግበሪያዎችን አገልግሎት እንዳይሰጡ ማድረግ ነው። ይህ ዓይነት እርምጃ በአምባገነን መንግሥታት የሚወሰደው በአገሪቱ ውስጥ በመሪው አካል የሚወሰዱ ሕግን የጣሱ እርምጃዎች ወደ ሚድያ ወጥተው ለዓለም እንዳይደርሱ ነው። የተለያዩ የሰብኣዊ መብት አራማጆችም ምርጫው ይህ ግድፈት ታየበት፣ መንግሥት ይህን አስሯል፣ ምርጫውን አጭበርብሯል እና አደባባይ ወጥተን ደምፃችንን ማሰማት አለብን የሚሉ መልዕክቶች ከማስተላለፍ ይልቅ፣ መንግሥት ይህን ደረገጽ ዘግቷል፣ ይህን ሚድያ አፈነ ከማለት ውጪ ስለምርጫው ወቅታዊ ሁኔታ እንዳይከታተሉ አድርጓቸዋል።

Sunday, September 4, 2016

የቂሊንጦ ወኅኒ ቤት ቃጠሎ ጉዳይ…

በናትናኤል ፈለቀ
(አርታኢ፤ በፍቃዱ ኃይሉ)

በምርጫ 1997 ማግስት የአደባባይ አመፆች ተበራክተው ነበር፡፡ በጥቅምት 24፣ 1998 አዲስ አበባ በሕዝባዊ አመፅ ስትናወጥ፣ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውስጥም ሊሰጠው ይገባው የነበረውን ያክል ትኩረት ሳያገኝ ያለፈ ትራጄዲ ተከስቶ ነበር፡፡ በወቅቱ እልፍ በኦ.ነ.ግ. ሥም ተወንጅለው የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች የቃሊቲ ግቢ ውስጥ ታጉረው ነበር፡፡ ታዲያ ግቢው ውስጥ በተፈጠረው ግርግር ‹ሊያመልጡ ሞክረዋል› በሚል 163 የሚደርሱ ታራሚዎች በተተኮሰባቸው ጥይት ሕይወታቸውን አጥተው ነበር፤ መንግሥት የሟቾቹ ቁጥር ዐሥር እንኳን እንደሚሞላ አላመነም ነበር፡፡

‹ሻዕቢያ› በቂሊንጦ እና ቃሊቲ ወኅኒ ቤቶች እጅግ ዝነኛ ሥም ነው፡፡ ‹ሻዕቢያ› በሚባል ቅፅል ሥም የሚጠራው የዋርድያዎች ኃላፊ፣ በቂሊንጦ የሚገኙ ተመላላሽ እስረኞች በፍርሐት ይርዱለታል፡፡ ‹ሻዕቢያ› ከ1998ቱ የቃሊቲ እስረኞች እልቂት ጋር ሥሙ በተደጋጋሚ ይነሳል፡፡ በወቅቱ የተነሳውን ግርግር ተከትሎ አግድም በመተኮስ ለብዙ እስረኞች እልቂት ምክንያት የሆነው ይኸው ‹ሻዕቢያ› የተባለ ግለሰብ እንደሆነ ይነገራል፡፡ በወቅቱ ቃሊቲ እስር ላይ የነበሩ ሰዎች እንደሚናገሩት፣ ሊፈቱ ጥቂት ቀናት የቀራቸው ሰዎች ሳይቀሩ ክፍላቸው በተቀመጡበት ለሞት ተዳርገዋል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ አግድም የተተኮሰው ጥይት ክፍላቸው ውስጥ አርፈው የተቀመጡትን እስረኞች የወኅኒውን የቆርቆሮ ግድግዳዎች እየበሳ በተቀመጡበት ጭንቅላታቸውን ስለመታቸው ነው፡፡ (‹ሻዕቢያ› በዚህ ዓመት አጋማሽ በከባድ የውንብድና ወንጀል ተጠርጥሮ ከሥራ ታግዷል)

ይህ በሆነ ማግስት እና በተከታዩ ሳምንት የቤተሰብ መጠየቂያው አጥር የቀብር ቦታ ይመስል እንደነበር በወቅቱ እዚያ የነበሩ ሰዎች ተናግረዋል፡፡ በወቅቱ እስረኛ ቤተሰብ የነበረው ሰው ሁሉ ይመጣና ‹እከሌን አስጠሩልኝ› ሲል የሞት መርዶ ይመለስለት እና ‹ዋይታ› መጠየቂያውን ቦታ ያጥለቀልቀው እንደነበር በሐዘን ያስታውሳሉ፡፡


‹ዋይታ› ራሱን ደገመ!

ዛሬ (ነሐሴ 29፣ 2008) ቂሊንጦ የታሰሩ ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ሊጠይቁ የሔዱ ሰዎች እስረኞቹ ሁሉ የሉም የሚል መልስ እየተሰጣቸው በዋይታ እና ለቅሶ እየታጠቡ ግማሾቹ ተስፋ ባለመቁረጥ እዚያው አካባቢ በፖሊስ እየተዋከቡ ሲቆዩ፣ ቀሪዎቹ መሔጃ በማጣት እና በተስፋ መቁረጥ ወደቤታቸው እየተመለሱ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ መንስዔ ትላንት በወኅኒው ግቢ የተነሳው ከፍተኛ የእሳት አደጋ ነው፡፡

ቅዳሜ (ነሐሴ 28 ቀን 2008) ጠዋት 2፡30 ጀምሮ እስከ 10፡00 ሰዐት ድረስ ቂሊንጦ የሚገኘው ‹በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች የአዲስ አበባ የቀጠሮ እስረኞች ማቆያ› በእሳት ተያይዞ ሲነድ እና ከባድ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ ውሏል፡፡ በወቅቱ የተነሱ የምስል ማስረጃዎች እደሚያረጋግጡት እና በወቅቱ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች እንዳስረዱት እሳቱ ከፍተኛ በሚባል ደረጃ ሲነድ እና ከውስጥ የፍንዳታ ጩኸትም ይሰማ እንደነበር፣  ጭሱ እስከ 10 ኪሎ ሜትር የሚደርስ ርቀት ላይ ሲታይ እንደነበር ነው፡፡


የአደጋው ሪፖርት

የእሳት አደጋውን የአገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛ እየተከታተሉት ሲዘግቡ ውለዋል፡፡ በገዢው ፓርቲ አባላት የሚዘወረው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በድረ-ገጹ እንደዘገበው በአደጋው ምክንያት አንድ ሰው እንደሞተ እና እሳቱን በቁጥጥር ሥር ለማዋል በቦታው የተገኙ 3 ‹የአዲስ አበባ ከተማ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከል እና መቆጣጠር ባለሥልጣን› ባልደረቦች ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው፤ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬትን ጠቅሶ ዘግቧል (በምሽት የሬድዮ ዘገባው ቀላል ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ቁጥር 6 አድርሶታል)፡፡ ሪፖርተር ጋዜጣም በዘገባው እሳቱ እስረኞች ማቆያ ግቢ ውስጥ ከሚገኝ የመመገቢያ ቦታ (ካፌ) እንደተነሳ እና ዞን 3 ድረስ ደርሶ እንደ ነበር በሥም ያልጠቀሳጨውን ምንጮች ጠቅሶ ዜና የሠራ ሲሆን እስረኞች ለማምለጥ ሙከራ ከማድረግ እዲቆጠቡ የማረሚያ ቤት ፖሊሶች ለማስፈራራት ወደ ሰማይ ሲተኩሱ ነበር ብሏል፡፡ ገዥውን ፓርቲ የተመለከተ ካልሆነ የፖለቲካ ዘገባ ሲሠራ የማይታወቀው እና በእግሊዘኛ ቋንቋ የሚታተመው ሳምንታዊው ፎርቹን ጋዜጣም አደጋውን በመከታተል ሲዘግብ እሳቱ ሆን ተብሎ በታራሚዎች የማምለጥ ሙከራ የተቀሰቀሰ እንደሆነ በድረ-ገጹ አስነብቧል፡፡ ፎርቹን ማምሻውን የድረ-ገጹ ዘገባ ላይ አዲስ መረጃ ሲያክል ‹20 የሚደርሱ ታሳሪዎች ተተኩሶባቸው እንደሞቱ› ዘግቧል፡፡ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ቴሌቭዥን አደጋውን እስረኞች ያስነሱት አድርጎ ዘግቧል፡፡

የእሳት አደጋው ሲደርስ በእሰረኞች ማቆያ አካባቢው የነበሩ የእስረኛ ቤተሰቦች እና ታዛቢዎች እሳቱ የተነሳው የቤተሰብ መጠየቂያ ሰዐት ከመድረሱ በፊት እንደነበር እና ጭሱ ጎልቶ መታየት ከመጀመሩ በፊት የማረሚያ ፖሊሶች ከቦታው እንዳስለቀቋቸው ይናገራሉ፡፡ ማምሻውን የኦሮሞ መብት ተከራካሪው ጃዋር መሐመድ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ‹22 የታሸጉ አስከሬኖችን ከቂሊንጦ ወኅኒ እንደተረከበ እና አስከሬኖቹ በወታደር እየተጠበቁ እንደሆነ› መረጃ እንደደረሰው ዘግቧል፡፡ ለአደጋው ሽፋን የሰጠው የበይነ-መረቡ ሬድዮ ዋዜማ በበኩሉ አካባቢው ላይ ከነበሩ የዓይን እማኞች አገኘሁ ያለውን መረጃ ጠቅሶ የማረሚያ ፖሊሶች ከመጠበቂያ ማማ ላይ ሆነው ወደ እስረኞች ሲተኩሱ እንደነበር ዘግቧል፡፡


የቂሊንጦ ወኅኒ ቤት ገጽታ

ቂሊንጦ የሚገኘው የአዲስ አበባ የቀጠሮ እስረኞች ማቆያ የፍርድ ቤት ጉዳያቸውን በእስር ላይ ሆነው የሚከታተሉ 3,100 በላይ የሚሆኑ ወንድ እስረኞች የሚገኙበት ሲሆን፣ በአራት ዞኖች የተከፋፈለ ነው፡፡ ከአራቱ ዞኖች መካከል ሦስቱ እያንዳንዳቸው ለእስረኞች የትኩስ መጠጥ አገልግሎት የሚሰጡበት አነስተኛ ካፌ ያላቸው ሲሆን፣ እነዚህ ካፌዎች ለማብሰል (ለማፍላት) የሚጠቀሙት የኤሌክትሪክ ኃይል ነው፡፡ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ዞን 4 በቅጣት ምክንያት ከሌሎች እስረኞች እዲገለሉ የተወሰነባቸው እስረኞችን ማቆያ ነው፡፡ በዚህ ዞን ውስጥ ካፌ የለም፡፡ ዞን 1፣ 2 እና 3 እያንዳንዳቸው 130 የሚጠጉ እስረኞችን የሚያሳድሩ ስምንት-ስምንት ክፍሎች ሲኖሯቸው፣ ዞን 4 ውስጥ ሁለት የእስረኛ ማቆያ ቤቶች ይገኛሉ፡፡

እስር ቤቱ በቀን ሦስት ግዜ ለእስረኞች ምግብ ያቀርባል፡፡ ይህ ምግብ የሚበስለው በተለምዶ እስረኞች ሜንሲ ቤት ብለው የሚጠሩት ከዞኖቹ ተገልሎ ካለ ቦታ ሲሆን ምግብ የሚታደልበት ሰዓት ሲደርስ ከየቤቶቹ ውስጥ በወር አነስተኛ ክፍያ የሚከፈላቸው በተለምዶ ሰፌድ እና ጎላ ሠራተኞች ተብለው የሚጠሩ እስረኞች ሜንሲ ቤት ድረስ በመሔድ ምግቡን እስረኞች ክፍል ድረስ ተሸክመው ያመጣሉ፡፡

እስር ቤቱ ውስጥ ሲጋራን ጨምሮ ማንኛውንም ዓይነት አደንዛዥ ዕፅ መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡ ሆኖም ሱስ ያለባቸው እስረኞች በዋነኝነት ከማረሚያ ፖሊሶች ጋር በመመሳጠር ሲጋራና አጤፋሪስን የመሳሰሉ አደንዛዥ ዕፆች አስገብተው ይጠቀማሉ፡፡ እነዚህን ዕፆችን በእስር ቤቱ ውስጥ ለማስገባት እና ለማከፋፈል በአንዳንድ እስረኞች መካከል ከፍተኛ የሆነ የቡድን ፀብ የሚያስነሳ ፉክክር የሚካሔድ ሲሆን ከኮንትሮባንድ ንግዱም የሚገኘው ገቢ እጅግ ከፍተኛ ነው (የአንድ ኒያላ ሲጋራ ዋጋ ቢያንስ 20 ብር ነው)፡፡

ዕፅ ለማጨስ መለኮሻ የሚሆን እሳት ለማግኘት ከፍተኛ ችግር ስላለ፣ የተለያዩ አልባሳትን ቀዶ በመግመድ ወይንም ለመተኛ ከሚገለገሉበት ፍራሽ ስፖንጅ በመቅደድ እና በማያያዝ አንዴ የተገኘውን እሳት ለቀናት ሳይጠፋ ያቆዩታል፡፡

በአሁኑ ወቅት እስር ቤቱ ውስጥ በመላው ኦሮሚያ እየተካሔደ ካለው የፀረ-አምባገነን ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ታስረው የሽብር ክስ የተመሠረተባቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት  አቶ በቀለ ገርባ እና የመብት ተሟጋቹ ዮናታን ተስፋዬ፣ የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ሽፈራው እና የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የነበሩ ሌሎች ወጣቶች፣ በሚያዝያ 2006 የታሰሩት ኦሮሞ ተማሪዎች እና ወደኤርትራ ሊኮበልሉ ሲሉ ተያዙ የተባሉት የአየር ኃይል ጓዶች (በእነመቶ አለቃ ማስረሻ መዝገብ) እንዲሁም ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ እስረኞ ይገኛሉ፡፡

በቃጠሎውና በተኩሱ ምክንያት የተጎዱ እስረኞች ቁጥር ስንት እንደሆነና ጉዳት የደረሰባቸው እስረኞች ማንነት ባለመገለጹ ምክንያት፣ እንዲሁም እስረኞቹ ወደሌላ ወኅኒ ቤት ተዛውረዋል በሚል ቤተሰቦች የዘመዶቻቸውን ደኅንነት ባለማረጋገጣቸው በእስር ቤቱ ውስጥ ወዳጅ ዘመድ ያላቸው ሰዎች ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብተዋል፡፡ በፖለቲካ እስረኞች ላይ የደረሰ ጉዳት ካለ ወይንም ስለ ደኅንነታቸው ማረጋገጫ መንግሥት የማይሰጥ ከሆነ ከፍተኛ አፀፋዊ የሕዝባዊ የአመፅ እርምጃ እንደሚወስዱ የኦሮሞ መብት አራማጆች ትላንት ማምሻውን ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል፡፡

እያገባደድን ባለው ዓመት ሕዳር 21 ቀን በጎንደር በሚገኝ እስር ቤት ውስጥ በተነሳ እሳት17 ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል፡፡

Sunday, June 26, 2016

የስቃይ ሰለባዎች


በዞን ዘጠኝ

ዓለማቀፍ የማሰቃየት ተግባር ተጠቂዎችን የመደገፍ ቀን (International Day in Support of Victims of Torture) ከጎርጎሮሳዊያኑ 1998 ጀምሮ በየዓመቱ ጁን 26 ቀን ይከበራል፡፡ ቀኑ ጁን 26 ላይ የሚከበርበት ሁለት ምክንያቶች ሲኖሩ፤ አንደኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር በመስራች አባል አገራት ቻርተሩን የፈረሙበት ቀን ጁን 26 1945 ሲሆን በሁለተኝነት የተባበሩት መንግስታት የፀረ ማሰቃየትና የጭካኔ የቅጣት ተግባር ኮንቬንሽን (Convention against Torture and Other Cruel, Inhuman or Degrading Treatment or Punishment) ወደ ስራ የገባው ጁን 26 1987 በመሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የቻርተሩም መስራች ፈራሚ ስትሆን ኮንቬንሽኑን ደግሞ በፓርላማ አጽድቃ ተቀብላለች፡፡

Torture’ በSergei Tunin


የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ የማሰቃየት ተግባር እንደሚፈፅም ለሚቀርብበት ትችት በጥቅሉ ‹‹ውሸት ነው›› ከማለት ውጭ ሁኔታዎቹን ለማሻሻል ምንም አይነት እርምጃ እየወሰደ ካለመሆኑም በላይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ ነገሮች እየተባባሱና በተለይም የፖለቲካ እስረኞች ላይ ጠንክረው ቀጥለዋል፡፡ እኛም በኢትዮጵያ ያለውን የማሰቃየት ተግባር ስፋት ያሳያል ይሆናል በሚል መነሻ ቀኑ የሚከበርበት ጁን 26 ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ በፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ አማካኝነት ክስ ተመስርቶባቸው ታስረው የሚገኙና ታስረው የነበሩ ግለሰቦች የደረሰባቸውን የማሰቃየት ተግባራት ራሳቸው በተለያዩ ጊዜያት እንደተረኩት በማሰባበሰብ እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፡፡

የተራኪዎቹን ማንነት በጽሁፉ ግርጌ ላይ ያገኙታል፡፡


Saturday, May 28, 2016

የግንቦት 20 ፍሬዎች




ቤተል ፋንታሁን የ25 ዓመት ወጣት ስትሆን፣ በኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ዘመን ተወልዳ ያደገች ነች፡፡ በሌላ አነጋገር አንዳንዶቹ ‘The EPRDF Generation’ የሚሉት ትውልድ አባል ናት፡፡ ቤተል ብቻ ሳትሆን ስልሳ አምስት በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ ኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ. ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ወዲህ የተወለዱ ሲሆን፣ ይሄም ከአገሪቱ አጠቃላይ ሕዝብ ሁለት ሦስተኛውን ይሸፍናል፡፡ ቤተል በዚህ ዕድሜዋ “እውነተኛው የግንቦት 20 ፍሬ ግንቦት 7 ብቻ ነው፤ ሌላው ሁሉ ግንቦት 20 ቢኖርም ባይኖርም መኖሩ አይቀርም” ትለናለች፡፡ አንብቧት፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ)ን 6 ወራት ዕድሜ አንሰዋለሁ፤
ድንገት ቸኩሎ ገብቶ ነው እንጂ ይደርስብኝ ነበር። እኔ ተረግዤ  የጎተራው ሼል ይሁን ተቀጣጣይ ነገር (ግንቦት 27፣ 1983) ፈንድቶ ሕዝቤ ሸሽቶ እኛ ሰፈር መጣ አሉ፡፡ ታዲያ አንዳንዶች ሲያሾፉብንየዛኔ ጥለውሽ ነው ያገኘንሽ ብለው ያወራሉ”፡፡ የኛን ሰፈር እወደዋለሁ፡፡ ግንቦት 20 ከሚባለው 2 ደረጃ ትምህርት ቤት ውጪ ኢሕአዴግ ለኛ ሰፈር ያደረገው ነገር የለም፡፡  ምህርት ቤቱም፣ ሰፈሩም በ97 ምርጫ ማግስት በተያዘብን ቂም ምክንያት 50 ዓመታት በላይ ያሳለፈ ሰፈር ባለፈው ዓመት ነውኮብልሰቶን› የገባበት፡፡ እንዲያውም ከአንዳንድ ሰዎች ጋር ተማክሬ UNESCO ላይ ለስመዘግበው ስል ለጥቂት ነው የቀደሙኝ። እሱ ይገርማችሁዋል፡፡ የቀድሞው የኢሕአዴግ ጠቅላይ ሚኒስትርየመረሸ› ጊዜ እንኳን ብቸኛው ድንኳን ያልተጣለበት ሰፈር ነው፤ የኛ ሰፈር፡፡ ይሄን ሰማን ብለው ደግሞ የያኔውን ዛሬ እንዳይመጡ።ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” ትሉኝ ይሆናል፡፡ አዎ እዚሁ አዲስ አበባ፡፡

የግንቦት 20 ፍሬ፡ 1

ምርጫ ‘97, ‘02, ‘07

1997 - እንደዛኔ 18 ዓመቴ እንዲሆን የተመኘሁበት ጊዜ የለም:: የዛኔ 8 ክፍል ሚኒስትሪ ተፈታኝ ነበርኩ:: በላያችን ላይ የተኩስ እሩምታ ሲወርድአንፈተንም› ብለን ፈተናው 30 ደቂቃ ዘገየ። እንዲህ እንዲህ እያልን 1998 ላይ ሁለቴ ምህርት ቤቱን አዘጋነው፡፡ በሁለተኛው በፌደራል ተገረፍን፡፡ ሰፈሬን የምወድበት አንዱ ምክንያት የሰፈሬ ልጆች ያኔ ‹ልጆቹን አናስነካም› ብለው ለፖሊሶቹ መንገድ መዝጋታቸውን ሳስበው ነው፡፡ የዛኔ ቤት ሲፈተሽ ኮርኒስ አልቀራቸውም።ወንድ አይትረፍ› የተባለ ይመስል የሰፈሬ ወንዶች ሁሉ ተለቅመው እስር ቤት ገቡ። 2002 ሞራላችን ዝቅ አለ፤ አሽቆለቆለ ሁለት ጣት የልለ፣ አምስት ጣት የለ፡፡ 2007 መቶ ፐርሰንት በልሉን፡፡ ለነገሩ ምርጫ አልነበረም ማለት ነው እኮ፡፡ ፓርላማው ውስጥ  ራሱ ምን እንደሚያደርጉ አላውቅም ልላችሁ ነበር፤ ግን ሳስታውሰው ለካስቤርጎ› ሆኗል፡፡ ዕድሜ ለፌስቡክ ይሁን።

የግንቦት 20 ፍሬ፡ 2

“አንድ ፓርቲ ገዢ ሆኖ አገር ሲመራ ማድረግ ያለባቸው 10 ነጥቦችብዬ ለመዘርዘር አሰብኩና 10 ነጥቦችን ደረደርኩ ለካስ ብዙ ነገር ተደርጎልናል መንገድ፣ ኮንዶሚንየም (ሊያውም ምትሃተኛ)፣ ባቡር ከነመንገዱ:: ግን መንግሥት ይህን ካልሠራ ታዲያ ምን ሊያደርግ ነው? መቼም ከኔ ጋር ቁጭ ብሎቃና› ቴሌቪዥንን አያይ። መንገድ ተሠራ እልልታ፡፡ ቤት ተሠራ እልልታ፡፡ ቆይ ልጠይቃችሁ አለቃ ወይ አስተማሪ አላችሁ እንበል፣ የሆነ ሥራ ተሰጣችሁ፣ ካልሠራችሁ ትባረራላችሁ፡፡ አለቀ በቃ፡፡ ኢሕአዴግም እንዳናባርረው ነው የሚሠራው እሱንም ሠራ ከተባለ (ሽርሽር እንሂድ ብለው ጓሮ እንደሚያዞሩት ሕፃን) የምር ለኛ አስቦ የሚመስለው ሰው ካለ እንተዋወቅ።