Tuesday, April 28, 2015

ስቃይና መብት ጥሰት - አስማማው ሐይለጊዬርጊስ

አስማማው ሐይለጊዬርጊስ 
ስቃይና መብት ጥሰት ያደረሱብኝ ሰዎቸ ስም ዝርዝር ( ሁሉም የፌደራል ፓሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል አባላት) በተለይ ስማቸው የማላውቃቸው ማንነታቸውን ለመናገር ፍቃደኛ ያልሆኑ አራት መርማሪዎች እና መርማሪ ጽጌ መርማሪ መኮንን አብተው

ዋና ዋና የማሰቃየት ተግባር የተፈጸመበት ቀንና ሰአት - ሚያዝያ 17 እስከ ሃምሌ 11 /2006 አም 

የማሰቃየት ተግባራት የተፈጸመበት ቦታ - የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ህንጻ ላይ

ዋና ዋና ማሰቃየት ተግባራት
- ከአንድ ወር ከአስራም አምስት ቀን በላይ የተፈጥሮ ብርሃን የሌለው በጨለማ ክፍል ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ታስሬያለሁ

- የቀለም አብዮት ልታመጣ ነው የወጠንከው በሚል ስለቀለም አብዬት እቅድ ተደጋጋሚ ተጠይቄያለሁ፡፡

- ስታሰር ከመንገድ ላይ የታፈንኩ ሲሆን ምንም አይነት ጥያቄ አንድጠይቅ አልተፈቀደልኝም፡፡ የእስር ትእዛዝ አላሳዬኝም ፣ የእስር ትእዛዝ አሳዬኝ ብዬ ብጠይቅም መልስ አልተሰጠኝም፡፡

- ባለብኝ የወገብ ህመም የተነሳ ወንበር አንዲገባልኝ ብጠይቅም ለ65 ቀናት ከፍተኛ ህመም ስር ሆኜ ቆይቻለሁ ፡፡ አካላዊ ጤንነት የመጠበቅ መብቴ ተነፍጓል፡፡

- “የአንተ ነገር አልቆለታል ፡፡ነጻ ሰው ነኝ ማለት አትችልም ወንጀልህን ተናዘዝ” የሚል ረጅም ሰአት ማስፈራሪያ ደርሶብኛል

- የሙያ ባልደረቦቼን ውብሸትን ታዬን እና ሌሎች ታራሚዎችን መጠየቄን አንደወንወጀል ተቆጥሮ ለምን ጥሩ ታራሚዎችን አትጠይቀም በሚል ከፍተኛ ተሳልቆ ደርሶብኛል፡፡

- በር በሌለው መጸዳጃ ቤት ለመጠቀም የተገደድን ሲሆን በቀን ለ10 ደቂቃ ብቻ ጸሃይ ብርሃን አገኝ ነበር ፡፡

- ስድብ መሳለቅ ያንተ ነገር ያለቀለት ጉዳይ ነው በማለት ከፍተኛ ስፓርት አንድሰራ እና የዞን9 አባል ነኝ ብዬ አንዳምን ከፍተኛ ማሰቃየት ደርሶብኛል ፡፡

- በካቴና ታስሬ እየተመረመርኩ ቢሆንም አንተ ጭራሽ ተመርማሪ አትመልስልም በሚል ተራ ምክንያት ማሰቃየት እና ጥፊ የተለመደ ነበር ፡፡

*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው  

No comments:

Post a Comment