Tuesday, February 3, 2015

የዞን 9 ጦማርያን አና ጋዜጠኞች ለ17ተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ለ16 ጊዜ ያህል ለስድስት ወራት ፍርድ ቤት የተመላለሱት እና ለ9 ወራት በእስር የሚገኙት የዞን9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ዛሬ ለ17ተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል ፡፡
በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ ተከሳሾች የእምነት ክህደት ቃላቸውን አንዲሰጡ የተጠበቀ ቢሆንም በተቃራኒው ተከሳሾች አቤቱታ አለን አቤቱታችን የእምነት ክህደት ቃል ከመስጠታችን በፌት መቅደም አለበት ብለው ተከራክረዋል፡፡ ዳኛው ዛሬ የእምነት ክህደት ቀጠሮ ነው ሌላ አቤቴታ አንቀበልም ቢሉም ፍርድ ቤቱ የራሱን ቃል አጥፏል ስለዚህም የመሃል ዳኛው አፋጣኝ ፍትህ የማግኘት መብታችንን ስለነፈጉን እንዲሁም ራሱ ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ትእዛዝ ሽሮ ያልተሻሻሉ ክሶችን በማካተት መከላከል የማንችልበት ሁኔታ ላይ ስላስቀመጡን መሃል ዳኛው የፍትህ ሂደቱን ዳኛ ሸለመ በቀለ ከቦታቸው ካልተነሱልን የእምነት ክህደት ቃላችንን ለመስጠት አንቸገራለን የሚል አቤቱታቸውን አቅርበዋል ፡፡
በዚህም መሰረት አቤቱታው ያልተጠበቀ የሆነባቸው ዳኛ የመገረም ፌት ያሳዬ ሲሆን አቤቱታው ላይ ለመወሰን ለነገ ጠዋት በ3 ሰአት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ችሎቱ ነገ ጠዋት ለ18ተኛ ጊዜ ደግሞ ይሰየማል፡፡


No comments:

Post a Comment